Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዮዲት የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ቸብ​ቸቦ እንደ ቈረ​ጠች

1 በመ​ሸም ጊዜ አሽ​ከ​ሮቹ ፈጥ​ነው ሰውን አስ​ወጡ፤ ባግ​ዋም ከወደ ውጭ በላ​ያ​ቸው ድን​ኳ​ኑን ዘጋ፤ በጌ​ታ​ውም ፊት የቆሙ አሽ​ከ​ሮ​ቹን አስ​ወ​ጥቶ ሰደ​ዳ​ቸው፤ ፈጽ​መው ስለ​ጠጡ ሁሉም ደክ​መ​ዋ​ልና ወደ ማደ​ሪ​ያ​ቸው ገቡ።

2 ዮዲ​ትም ብቻ​ዋን በድ​ን​ኳን ውስጥ ከሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ጋር ቀረች፤ እርሱ ግን አብ​ዝቶ ወይን ስለ​ጠጣ ሰክሮ በአ​ል​ጋው ላይ ተኝቶ ነበር።

3 ዮዲ​ትም አገ​ል​ጋ​ይ​ዋን ወደ ውጭ ወጥታ በማ​ደ​ሪ​ያዋ ትቆም ዘንድ አዘ​ዘ​ቻት፤ “ወደ​ም​ጸ​ል​ይ​በት እወ​ጣ​ለሁ” ብላ​ታ​ለ​ችና እንደ ወት​ሮው በም​ት​መ​ጣ​በት ጊዜ ትጠ​ብ​ቃት ዘንድ አዘ​ዘ​ቻት፤ ለባ​ግ​ዋም እን​ደ​ዚሁ ነገ​ረ​ችው።

4 ሁሉም ከእ​ር​ስዋ ዘንድ ወጡ፤ ታና​ሽም፥ ታላ​ቅም ቢሆን በእ​ል​ፍኙ የቀረ አል​ነ​በ​ረም። ዮዲ​ትም ተነ​ሥታ በመ​ኝ​ታው አጠ​ገብ ቆመች። በል​ቧም፥ “የኀ​ይል ሁሉ አም​ላክ አቤቱ፥ ይህን ነገር እይ፤ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ከፍ ከፍ ትል ዘንድ በዚች ሰዓት በእኔ እጅ ኀይ​ል​ህን አድ​ርግ።

5 ርስ​ት​ህን ታነሣ ዘንድ ጊዜው ደር​ሷ​ልና በእኛ የተ​ነሡ ጠላ​ቶች ይጠፉ ዘንድ አሳ​ቤን ሁሉ ፈጽ​ም​ልኝ” አለች።

6 ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም መኝታ ወደ ትራሱ ሄደች፤ የራ​ስጌ ሰይ​ፉ​ንም መዘ​ዘች።

7 በራ​ስ​ጌ​ውም ቆመች፤ የራ​ሱ​ንም ጠጕር ይዛ “የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ አቤቱ፥ ዛሬ አጽ​ናኝ” አለች።

8 በኀ​ይሏ ሁለት ጊዜ አን​ገ​ቱን መታ​ችው፤ ራሱ​ንም ቈረ​ጠ​ችው።

9 ሬሳ​ው​ንም ከመ​ኝ​ታው ወደ ምድር ጣለ​ችው፤ የራ​ስጌ መጋ​ረ​ጃ​ው​ንም ከም​ሰ​ሶው አወ​ረ​ደች፤ ጥቂ​ትም ዐረ​ፈች፤ ወጥ​ታም ለብ​ላ​ቴ​ናዋ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ቸብ​ቸቦ ሰጠ​ቻት።


ዮዲት ወደ ቤጤ​ልዋ እንደ ተመ​ለ​ሰች

10 እህል በም​ት​ይ​ዝ​በት ከረ​ጢ​ትም ጨመ​ረ​ችው፤ ለጸ​ሎት እን​ዳ​ስ​ለ​መዱ ሁለቱ ሁሉ በአ​ን​ድ​ነት ወጡ፤ ከሰ​ፈ​ሩም አል​ፈው ወደ ሸለ​ቆው ዞሩ፤ ወደ ቤጤ​ልዋ ዐቀ​በ​ትም ወጡ፤ ወደ ከተ​ማ​ውም በር ደረሱ።

11 ዮዲ​ትም በሩቁ ሆና በር የሚ​ጠ​ብቁ ዘበ​ኞ​ችን፥ “ዛሬ ኀይ​ልን እን​ዳ​ደ​ረገ ዳግ​መኛ ለእ​ስ​ራ​ኤል በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው ላይ ጽና​ትና ኀይ​ልን ያደ​ርግ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእኛ ጋር አለና ክፈቱ፤ ክፈቱ” አለ​ቻ​ቸው።

12 ከዚ​ህም በኋላ የከ​ተ​ማው ሰዎች ቃል​ዋን በሰሙ ጊዜ ወደ ከተ​ማው በር ፈጥ​ነው ወረዱ፤ የከ​ተማ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችን ጠሩ።

13 እንደ ተመ​ለ​ሰ​ችም አድ​ን​ቀ​ዋ​ልና ታና​ሹም፥ ታላ​ቁም ሁሉ ሮጠው ሄዱ፤ በሩ​ንም ከፍ​ተው ተቀ​በ​ሏት፤ እሳ​ትም አን​ድ​ደው፥ ፋና አብ​ር​ተው ከበ​ቧት።

14 “ጠላ​ቶ​ቻ​ች​ንን በዚች ሌሊት በእጄ አጠ​ፋ​ቸው እንጂ ምሕ​ረ​ቱ​ንና ይቅ​ር​ታ​ውን ከእ​ስ​ራ​ኤል አላ​ራ​ቀ​ምና በታ​ላቅ ቃል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፤ አመ​ስ​ግ​ኑት። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ስ​ግ​ኑት” አለ​ቻ​ቸው።

15 ቸብ​ቸ​ቦ​ው​ንም ከከ​ረ​ጢቷ አው​ጥታ አሳ​የ​ቻ​ቸው፤ “የአ​ሦር ሠራ​ዊት አለቃ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ቸብ​ቸቦ እነሆ፥ በሚ​ጠጣ ጊዜ ተን​ተ​ር​ሶት የሚ​ተ​ኛ​በት ሰይ​ፉም እነሆ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእኔ በሴቷ አድሮ ገደ​ለው።

16 እን​ዲ​ሞት በመ​ልኬ አስ​ተው ዘንድ በሄ​ድ​ሁ​በት ጎዳና የጠ​በ​ቀኝ፥ በእ​ኔም ኀጢ​አ​ት​ንና በደ​ልን፥ መዋ​ረ​ድ​ንም ያላ​ደ​ረገ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕያው ነው” አለ​ቻ​ቸው።

17 ሕዝ​ቡም ሁሉ ፈጽ​መው አደ​ነቁ፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፈጽ​መው ሰገዱ፤ በአ​ን​ድ​ነ​ትም እን​ዲህ አሉ፥ “ዛሬ በዚች ቀን የወ​ገ​ኖ​ች​ህን ጠላ​ቶች ያጠ​ፋ​ሃ​ቸው አንተ አም​ላ​ካ​ችን ቡሩክ ነህ።”

18 ዖዝ​ያ​ንም እን​ዲህ አላት፥ “በዚህ ዓለም ከሚ​ኖሩ ሴቶች ይልቅ አንቺ ልጄ፥ ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የባ​ረ​ከሽ ነሽ። ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን የፈ​ጠረ፥ የጠ​ላ​ቶ​ቻ​ች​ንን አለቃ ቸብ​ቸቦ ትቈ​ርጪ ዘንድ የረ​ዳሽ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ክም ቡሩክ ነው።

19 ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ኀይል እያ​ሰቡ ምስ​ጋ​ናሽ ከሰው ልቡና አይ​ጠ​ፋ​ምና።

20 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይህን ለዘ​ለ​ዓ​ለም እን​ድ​ት​ከ​ብሪ ያድ​ር​ግ​ልሽ፤ ስለ ወገ​ኖ​ችሽ አንቺ ልሙት ብለሽ ወጣሽ እንጂ፥ በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት በቀ​ጥታ ሄድሽ እንጂ ለሰ​ው​ነ​ትሽ አል​ራ​ራ​ሽ​ምና በቸ​ር​ነቱ ይመ​ል​ከ​ትሽ።” ሕዝ​ቡም ሁሉ፥ “አሜን፥ አሜን” አሉ።

跟着我们:



广告