Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

መሳፍንት 21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ብን​ያ​ማ​ው​ያን ሚስ​ቶ​ችን እን​ዲ​ያ​ገኙ የተ​ደ​ረገ ምክር

1 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሰዎች፥ “ከእኛ ማንም ሰው ሴት ልጁን ለብ​ን​ያም ልጆች በጋ​ብቻ አይ​ስጥ” ብለው በመ​ሴፋ ተማ​ማሉ።

2 ሕዝ​ቡም ወደ ቤቴል መጥ​ተው በዚያ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እስከ ማታ ድረስ ተቀ​መጡ፤ ድም​ፃ​ቸ​ው​ንም ከፍ አድ​ር​ገው ጽኑዕ ልቅሶ አለ​ቀሱ።

3 እነ​ር​ሱም፥ “አቤቱ፥ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ሆይ፥ ዛሬ ከእ​ስ​ራ​ኤል አንድ ነገድ መታ​ጣቱ፥ ስለ​ምን ይህ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ሆነ?” አሉ።

4 በነ​ጋ​ውም ሕዝቡ ማል​ደው ተነሡ፤ በዚ​ያም መሠ​ዊያ ሠሩ፤ የሚ​ቃ​ጠ​ልና የደ​ኅ​ን​ነት መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም አቀ​ረቡ።

5 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ መሴፋ ስላ​ል​ወጣ ሰው፥ “እርሱ ፈጽሞ ይገ​ደል” ብለው ታላቅ መሐላ ምለው ነበ​ርና፥ “ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ ሁሉ ወደ ጉባኤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያል​ወጣ ማን ነው?” አሉ።

6 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ስለ ወን​ድ​ማ​ቸው ስለ ብን​ያም ልጆች አዝ​ነው እን​ዲህ አሉ፥ “ዛሬ ከእ​ስ​ራ​ኤል አንድ ነገድ ጠፍ​ቶ​አል።

7 እኛ ልጆ​ቻ​ች​ንን እን​ዳ​ን​ድ​ር​ላ​ቸው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምለ​ና​ልና የተ​ረ​ፉት ሚስ​ቶ​ችን እን​ዲ​ያ​ገኙ ምን እን​ድ​ርግ?”

8 እነ​ር​ሱም፥ “ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ መሴፋ ያል​ወጣ ማን ነው?” አሉ። እነ​ሆም፥ ከኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓድ ወደ ሰፈሩ ወደ ጉባ​ኤው ማንም አል​ወ​ጣም ነበር።

9 ሕዝ​ቡም በተ​ቈ​ጠሩ ጊዜ፥ እነሆ፥ ከኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓድ ነዋ​ሪ​ዎች ሰው አል​ተ​ገ​ኘም።

10 ማኅ​በ​ሩም ወደ​ዚያ ዐሥራ ሁለት ሺህ ኀያ​ላን ሰዎ​ችን ልከው፥ “ሂዱ በኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓ​ድም ያሉ​ትን ሰዎች ሴቶ​ች​ንም ሕዝ​ቡ​ንም በሰ​ይፍ ስለት ግደሉ።

11 የም​ታ​ደ​ር​ጉ​ትም ይህ ነው፤ ወን​ዱን ሁሉ፥ ወንድ የሚ​ያ​ው​ቁ​ት​ንም ሴቶች ሁሉ ፈጽ​ማ​ችሁ አጥፉ፤ ደና​ግ​ሉን ግን አት​ግ​ደ​ሉ​አ​ቸው፤” ብለው አዘ​ዙ​አ​ቸው፤ እን​ዲ​ሁም አደ​ረጉ።

12 በኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓድ በሚ​ኖሩ መካ​ከ​ልም ወንድ ያላ​ወቁ አራት መቶ ቆነ​ጃ​ጅት ደና​ግ​ልን አገኙ፤ በከ​ነ​ዓ​ንም ሀገር ወዳ​ለ​ችው ወደ ሴሎ ወደ ሰፈሩ አመ​ጡ​አ​ቸው።

13 ማኅ​በ​ሩም ሁሉ በሬ​ሞን ዐለት ወዳ​ሉት ወደ ብን​ያም ልጆች መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላኩ፤ በሰ​ላ​ምም ጠሩ​አ​ቸው።

14 በዚ​ያም ጊዜ የብ​ን​ያም ልጆች ወደ እስ​ራ​ኤል ልጆች ተመ​ለሱ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓድ ሴቶች ያዳ​ኑ​አ​ቸ​ውን ሴቶች ሰጡ​አ​ቸው። በዚ​ህም ተስ​ማሙ።

15 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ ውስጥ ስብ​ራት ስላ​ደ​ረገ ሕዝቡ ስለ ብን​ያም አዘኑ።

16 የማ​ኅ​በሩ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችም፥ “ከብ​ን​ያም ሴቶች ጠፍ​ተ​ዋ​ልና የቀ​ሩት ስዎች ሚስት እን​ዲ​ያ​ገኙ ምን እና​ደ​ር​ጋ​ለን?” አሉ።

17 ደግ​ሞም፥ “ከእ​ስ​ራ​ኤል አንድ ነገድ እን​ዳ​ይ​ደ​መ​ሰስ ከብ​ን​ያም ላመ​ለ​ጡት ርስት ይኑር።

18 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች፥ “ልጁን ለብ​ን​ያም የሚ​ሰጥ ርጉም ይሁን ብለው ምለ​ዋ​ልና እኛ ከል​ጆ​ቻ​ችን ሚስ​ቶ​ችን ለእ​ነ​ርሱ መስ​ጠት አን​ች​ልም” አሉ።

19 እነ​ር​ሱም፥ “እነሆ፥ በቤ​ቴል በመ​ስዕ በኩል፥ ከቤ​ቴ​ልም ወደ ሰቂማ በሚ​ወ​ስ​ደው መን​ገድ በም​ሥ​ራቅ በኩል በሌ​ብና በዐ​ዜብ በኩል ባለ​ችው በሴሎ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓል በየ​ዓ​መቱ አለ” አሉ።

20 የብ​ን​ያ​ም​ንም ልጆች እን​ዲህ ብለው አዘ​ዙ​አ​ቸው፥ “ሂዱ በወ​ይ​ኑም ስፍራ ተደ​በቁ፤

21 ተመ​ል​ከ​ቱም፤ እነሆ፥ የሴሎ ሴቶች ልጆች አታሞ ይዘው ለዘ​ፈን ሲወጡ ከወ​ይኑ ስፍራ ውጡ፤ ከሴሎ ሴቶች ልጆ​ችም ለየ​ራ​ሳ​ችሁ ሚስ​ትን ንጠቁ፤ ወደ ብን​ያም ምድ​ርም ሂዱ።

22 አባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ሊጣ​ሉ​አ​ችሁ ወደ እኛ በመጡ ጊዜ፦ ስለ እኛ ማሩ​አ​ቸው፥ እኛ ሚስት ለያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸው በሰ​ልፍ አል​ወ​ሰ​ድ​ን​ላ​ቸ​ው​ምና፥ እና​ን​ተም በደል ይሆ​ን​ባ​ችሁ ስለ ነበር አላ​ጋ​ባ​ች​ኋ​ቸ​ው​ምና፥” እን​ላ​ቸ​ዋ​ለን።

23 የብ​ን​ያ​ምም ልጆች እን​ዲሁ አደ​ረጉ፤ በቍ​ጥ​ራ​ቸ​ውም መጠን ከተ​ነ​ጠ​ቁት ዘፋ​ኞች ሚስ​ትን ወሰዱ፤ ወደ ርስ​ታ​ቸ​ውም ተመ​ል​ሰው ሄዱ፤ ከተ​ሞ​ች​ንም ሠር​ተው ተቀ​መ​ጡ​ባ​ቸው።

24 በዚያ ጊዜም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከዚያ ተነሡ፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዱም ወደ ወገ​ኑና ወደ ነገዱ ሄደ፤ ሰውም ሁሉ ከዚያ ወደ ርስቱ ተመ​ለሰ።

25 በዚ​ያም ዘመን በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ንጉሥ አል​ነ​በ​ረም፤ ሰው ሁሉ በፊቱ መል​ካም መስሎ የታ​የ​ውን ያደ​ርግ ነበር።

跟着我们:



广告