Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 38 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለኢ​ዮብ እንደ መለ​ሰ​ለት

1 ኤል​ዩስ ንግ​ግ​ሩን ካቆመ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በደ​መ​ናና በዐ​ውሎ ነፋስ ውስጥ ሆኖ ኢዮ​ብን ጠየ​ቀው፤ እን​ዲ​ህም አለው፦

2 “ከእኔ ምክ​ርን የሚ​ሸ​ሽግ፥ በል​ቡም ነገ​ርን የሚ​ደ​ብቅ ማን ነው? ከእኔ ይሰ​ው​ረ​ዋ​ልን?

3 እን​ግ​ዲህ እንደ ሰው ወገ​ብ​ህን ታጠቅ፤ እጠ​ይ​ቅ​ሃ​ለሁ፥ አን​ተም መል​ስ​ልኝ።

4 ምድ​ርን በመ​ሠ​ረ​ትሁ ጊዜ አንተ ወዴት ነበ​ርህ? ታስ​ተ​ውል እንደ ሆነ ንገ​ረኝ።

5 ብታ​ውቅ መስ​ፈ​ሪ​ያ​ዋን የወ​ሰነ፥ በላ​ይ​ዋስ የመ​ለ​ኪያ ገመ​ድን የዘ​ረጋ ማን ነው?

6 መሠ​ረ​ቶ​ችዋ በምን ላይ ተተ​ክ​ለው ነበር? የማ​ዕ​ዘ​ን​ዋ​ንስ ድን​ጋይ ያቆመ ማን ነው?

7 ከዋ​ክ​ብት በተ​ፈ​ጠሩ ጊዜ መላ​እ​ክቴ ሁሉ በታ​ላቅ ድምፅ አመ​ሰ​ገ​ኑኝ

8 ከእ​ናቷ ማኅ​ፀን በወ​ጣች ጊዜ፥ ባሕ​ርን በመ​ዝ​ጊ​ያ​ዎች ዘጋ​ኋት፤

9 ደመ​ና​ውን ልብስ አደ​ረ​ግ​ሁ​ላት። በጭ​ጋ​ግም ጠቀ​ለ​ል​ኋት።

10 ድን​በ​ርም አደ​ረ​ግ​ሁ​ላት። መወ​ር​ወ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ንና መዝ​ጊ​ያ​ዎ​ች​ንም አኖ​ርሁ።

11 እስ​ከ​ዚህ ድረስ ድረሺ፥ ከወ​ሰ​ን​ሽም አት​ለፊ፤ ነገር ግን ማዕ​በ​ልሽ በመ​ካ​ከ​ልሽ ይገ​ደብ አል​ኋት።

12 “የን​ጋት ወገ​ግታ በአ​ንተ ተፈ​ጥ​ሮ​አ​ልን? የአ​ጥ​ቢያ ኮከ​ብስ ትእ​ዛ​ዙን በአ​ንተ ዐው​ቋ​ልን?

13 የም​ድ​ርን ዳርቻ ይይዝ ዘንድ፥ ከእ​ር​ስ​ዋም ኃጥ​ኣ​ንን ያና​ውጥ ዘንድ።

14 አንተ ጭቃ​ውን ከመ​ሬት ወስ​ደህ ሕያው ፍጥ​ረ​ትን ፈጥ​ረ​ሃ​ልን? በም​ድ​ርስ ላይ እን​ዲ​ና​ገር አድ​ር​ገ​ሃ​ልን?

15 የኃ​ጥ​ኣ​ንን ብር​ሃ​ና​ቸ​ውን ከል​ክ​ለ​ሃ​ልን? የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ች​ንስ ክንድ ሰብ​ረ​ሃ​ልን?

16 ወደ ባሕር ምን​ጭስ ውስጥ ገብ​ተ​ሃ​ልን? በጥ​ል​ቁስ መሠ​ረት ውስጥ ተመ​ላ​ል​ሰ​ሃ​ልን

17 ከግ​ር​ማ​ህስ የተ​ነሣ የሞት በሮች ተከ​ፍ​ተ​ው​ል​ሃ​ልን? የሲ​ኦል በረ​ኞ​ችስ አን​ተን አይ​ተው ይደ​ነ​ግ​ጣ​ሉን?

18 ከሰ​ማይ በታች ያለ የም​ድ​ር​ንስ ስፋት አስ​ተ​ው​ለ​ሃ​ልን? መጠ​ኑም ምን ያህል እንደ ሆነ እስኪ ንገ​ረኝ!

19 “የብ​ር​ሃን ማደ​ር​ያው ቦታ የት ነው? የጨ​ለ​ማስ ቦታው ወዴት አለ?

20 ትችል እንደ ሆነ፥ መን​ገ​ዳ​ቸ​ው​ንም ታውቅ እን​ደ​ሆነ፥ ወደ ዳር​ቻ​ቸው እስኪ ውሰ​ደኝ።

21 በዚ​ያን ጊዜ ተወ​ል​ደህ ነበ​ርና፥ የዕ​ድ​ሜ​ህም ቍጥር ብዙ ነውና፥ በእ​ው​ነት አንተ ሳታ​ውቅ አት​ቀ​ርም።

22 በውኑ ወደ በረ​ዶው ቤተ መዛ​ግ​ብት ገብ​ተ​ሃ​ልን? የበ​ረ​ዶ​ው​ንስ ቅን​ጣት ቤተ መዛ​ግ​ብት አይ​ተ​ሃ​ልን?

23 ይህስ በጠ​ላ​ትህ ጊዜ ለሰ​ል​ፍና ለጦ​ር​ነት ቀን ይጠ​በ​ቅ​ል​ሃ​ልን?

24 አመ​ዳይ ከየት ይወ​ጣል? ከሰ​ማይ በታች ያለ የአ​ዜብ ነፋ​ስስ እን​ዴት ይበ​ተ​ናል?

25 ለኀ​ይ​ለ​ኛው ዝናብ መው​ረ​ጃ​ውን፥ ወይስ ለሚ​ያ​ን​ጐ​ዳ​ጕ​ደው መብ​ረቅ መን​ገ​ድን ያዘ​ጋጀ ማን​ነው?

26 ማንም በሌ​ለ​በት ምድር ላይ፥ ሰውም በማ​ይ​ኖ​ር​በት ምድረ በዳ ይዘ​ንም ዘንድ፥

27 ባድ​ማ​ው​ንና ውድ​ማ​ውን ያጠ​ግብ ዘንድ፥ ሣሩ​ንም በም​ድረ በዳ ያበ​ቅል ዘንድ፥

28 የዝ​ናብ አባቱ ማን ነው? ወይስ የጠ​ልን ነጠ​ብ​ጣብ የወ​ለደ ማን ነው?

29 በረ​ዶስ ከማን ማኅ​ፀን ይወ​ጣል? የሰ​ማ​ዩ​ንስ አመ​ዳይ ማን ወለ​ደው?

30 እር​ሱም እንደ ፈሳሽ ውኃ ይወ​ር​ዳል። ውኆች እንደ ድን​ጋይ ጠነ​ከሩ፥ የኃ​ጥ​ኣ​ን​ንስ ፊት ማን አዋ​ረደ?

31 “በውኑ የሰ​ባ​ቱን ከዋ​ክ​ብት ዘለላ ታስር ዘንድ፥ ወይስ ኦሪ​ዮን የሚ​ባ​ለ​ውን ኮከብ ትፈታ ዘንድ ትች​ላ​ለ​ህን?

32 ወይስ ማዛ​ሮት የሚ​ባ​ሉ​ትን ከዋ​ክ​ብት በጊ​ዜ​ያ​ቸው ታወጣ ዘንድ፥ ወይስ የም​ሽ​ቱን ኮከብ ከል​ጆቹ ጋር ትመራ ዘንድ ትች​ላ​ለ​ህን?

33 የሰ​ማ​ይን ሥር​ዐት፥ ከሰ​ማይ በታ​ችስ የሚ​ሆ​ነ​ውን ታው​ቃ​ለ​ህን?

34 ደመ​ና​ውን በቃ​ልህ ትጠ​ራ​ዋ​ለ​ህን? ብዙ ውኃስ እየ​ተ​ን​ቀ​ጠ​ቀጠ ይመ​ል​ስ​ል​ሃ​ልን?

35 መብ​ረ​ቁን ትል​ከ​ዋ​ለ​ህን? እር​ሱስ ይሄ​ዳ​ልን? ደስ​ታ​ህስ ምን​ድን ነው ይል​ሃ​ልን?

36 ለሴ​ቶች የፈ​ት​ልን ጥበ​ብና የተ​ለ​ያዩ የጥ​ልፍ ሥራ​ዎ​ችን ዕው​ቀት ማን ሰጠ?

37 የሰ​ማ​ይን ደመና በጥ​በቡ ሊቈ​ጥር የሚ​ችል ማን ነው? ሰማ​ይ​ንም ወደ ምድር ያዘ​ነ​በለ ማን ነው?

38 እንደ ትቢያ በም​ድር ተዘ​ር​ግቷል፤ እንደ ዓለት ድን​ጋ​ይም አጣ​በ​ቅ​ሁት።

39 “ለአ​ን​በ​ሳ​ዪቱ አደን ታድ​ና​ለ​ህን? የእ​ባ​ቦ​ች​ንስ ነፍስ ታጠ​ግ​ባ​ለ​ህን?

40 በዋ​ሾ​ቻ​ቸው ውስጥ ተጋ​ድ​መው በጫ​ካም ውስጥ አድ​ብ​ተው ይቀ​መ​ጣ​ሉና።

41 ልጆቹ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሲጮኹ፥ የሚ​በ​ሉ​ትም ፈል​ገው ሲቅ​በ​ዘ​በዙ፥ ለቍራ መብ​ልን የሚ​ሰ​ጠው ማን ነው?

跟着我们:



广告