Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 37 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 “ስለ​ዚ​ህም ልቤ ደነ​ገ​ጠ​ች​ብኝ፥ ከስ​ፍ​ራ​ዋም ተን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰች።

2 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የቍ​ጣ​ውን ድምፅ ስማ፥ ከአ​ፉም የሚ​ወ​ጣ​ውን ጕር​ም​ር​ምታ አድ​ምጥ።

3 እር​ሱን ወደ ሰማ​ያት ሁሉ ታች፥ ብር​ሃ​ኑ​ንም ወደ ምድር ዳርቻ ይሰ​ድ​ዳል።

4 በስ​ተ​ኋ​ላው ድምፅ ይጮ​ኻል፤ በግ​ር​ማ​ውም ድምፅ ያን​ጐ​ደ​ጕ​ዳል፤ ድም​ፁም በተ​ሰማ ጊዜ ሰዎች እን​ዲ​ጠፉ አያ​ደ​ር​ግም።

5 ኀያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በድ​ምፁ ድንቅ አድ​ርጎ ያን​ጐ​ደ​ጕ​ዳል፤ ለእ​ን​ስ​ሳት በየ​ጊ​ዜው ምግ​ባ​ቸ​ውን ያዘ​ጋ​ጃል፥ የሚ​ተ​ኙ​በ​ት​ንም ጊዜ ያው​ቃሉ፤ በዚህ ሁሉ ልብህ አይ​ደ​ን​ግ​ጥ​ብህ፤ ሥጋ​ህም ልብ​ህም ከግ​ዘፉ አይ​ለ​ወ​ጥ​ብህ፤ እር​ሱም እኛ የማ​ና​ው​ቀ​ውን ታላቅ ነገር ያደ​ር​ጋል።

6 በረ​ዶ​ው​ንና ውሽ​ን​ፍ​ሩን፥ ብር​ቱ​ው​ንም ዝናብ በም​ድር ላይ እን​ዲ​ወ​ርድ ያዝ​ዛል።

7 ሰው ሁሉ ደካ​ማ​ነ​ቱን ያውቅ ዘንድ፥ የሰ​ውን ሁሉ እጅ ያት​ማል።

8 አው​ሬ​ዎ​ቹም ወደ ጫካው ይገ​ባሉ፥ በዋ​ሾ​ቻ​ቸ​ውም ያር​ፋሉ።

9 ከተ​ሰ​ወረ ማደ​ሪ​ያ​ውም ችግር፥ ከተ​ራ​ሮች ጫፍም ብርድ ይመ​ጣል።

10 ከኀ​ያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እስ​ት​ን​ፋስ ውርጭ ይመ​ጣል። ውኃ​ው​ንም እንደ ወደደ ይመ​ራ​ዋል።

11 የተ​መ​ረ​ጡ​ትን በደ​መና ይሰ​ው​ራል፤ ብር​ሃ​ኑም ደመ​ና​ውን ይበ​ት​ናል፤

12 እር​ሱም ሰው በሚ​ኖ​ር​በት ዓለም ላይ፥ ያዘ​ዘ​ውን ሁሉ ያደ​ርግ ዘንድ፥ ፈቃዱ ወደ መራ​ችው ይዞ​ራል።

13 ይኸ​ውም፥ ለተ​ግ​ሣጽ ወይም ለም​ድሩ ወይም በም​ሕ​ረት ለሚ​ያ​ገ​ኘው እን​ዲ​ሆን ነው።

14 “ኢዮብ ሆይ፥ ይህን ስማ፤ ቁም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀይል ተገ​ሠጽ።

15 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራ​ውን እን​ዳ​ከ​ና​ወነ ከጨ​ለ​ማም ለይቶ ብር​ሃ​ንን እንደ ፈጠረ እና​ው​ቃ​ለን።

16 የደ​መ​ና​ትን ክፍ​ሎች፥ አስ​ፈሪ የሆ​ነ​ው​ንም የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞ​ችን አወ​ዳ​ደቅ ያው​ቃል።

17 የአ​ዜብ ነፋስ በተ​ኮሰ ጊዜ ያንተ ልብ​ስህ የሞቀ ነው። እን​ግ​ዲህ በም​ድር ላይ ፀጥ በል።

18 እንደ ቀለጠ መስ​ተ​ዋት ብርቱ የሆ​ኑ​ትን ሰማ​ያት ከእ​ርሱ ጋር ልት​ዘ​ረጋ ትች​ላ​ለ​ህን?

19 ስለ​ዚህ ንገ​ረኝ! ምን እን​ለ​ዋ​ለን? እን​ግ​ዲህ ዝም እን​በል፥ ብዙም አን​ና​ገር፥

20 “ሰው በእኔ ዘንድ ሲቆም ዝም እል ዘንድ፥ መጽ​ሐፍ ወይም ጸሓፊ አለ​ኝን?

21 “ብር​ሃን ለሁሉ የሚ​ታይ አይ​ደ​ለም ብር​ሃን በእ​ርሱ ዘንድ በደ​መና ውስጥ ሆኖ ከሩቅ በሰ​ማ​ያት ያበ​ራል።

22 ከሰ​ሜን እንደ ወርቅ የሚ​ያ​በራ ደመና ይወ​ጣል፤ በዚ​ህም ሁሉን የሚ​ችል የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታላቅ ክብ​ርና ምስ​ጋና አለ።

23 በኀ​ይል ከእ​ርሱ ጋር እኩል የሚ​ሆን፥ እው​ነ​ት​ንም የሚ​ፈ​ርድ ሌላ አና​ገ​ኝም። እርሱ እን​ደ​ማ​ይ​ሰማ ታስ​ባ​ለ​ህን?

24 ስለ​ዚህ ሰዎች ይፈ​ሩ​ታል፤ በል​ባ​ቸ​ውም ጠቢ​ባን የሆኑ ሁሉ ይፈ​ሩ​ታል።”

跟着我们:



广告