Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 35 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ኢዮብ ራሱን በማ​ጽ​ደቁ ኤል​ዩስ እንደ ተቃ​ወመ

1 ኤል​ዩ​ስም ደግሞ መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦

2 “አንተ ተዋ​ቅ​ሰህ ምን ትላ​ለህ? ወይስ፦ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እኔ ጻድቅ ነኝ የም​ትል አንተ ማን ነህ?

3 ኀጢ​አት ብሠ​ራስ ምን አደ​ር​ጋ​ለሁ? ትላ​ለህ።

4 እኔ ለአ​ን​ተና ለሦ​ስቱ ወዳ​ጆ​ችህ እመ​ል​ሳ​ለሁ።

5 ወደ ሰማይ ተመ​ል​ከት፥ እይም፤ ደመ​ናም ከአ​ንተ በላይ ምን ያህል ከፍ እን​ዳለ ዕወቅ።

6 ኀጢ​አት ብት​ሠራ በእ​ርሱ ላይ ምን ታደ​ር​ጋ​ለህ? ብዙም ብት​በ​ድል ምን ማድ​ረግ ትች​ላ​ለህ?

7 ጻድ​ቅስ ብት​ሆን ምን ትሰ​ጠ​ዋ​ለህ? ወይስ ከእ​ጅህ ምንን ይቀ​በ​ላል?

8 እንደ አንተ ያለ​ውን ሰው ክፋ​ትህ ይጎ​ዳ​ዋል፤ ለሰ​ውም ልጅ ጽድ​ቅህ ይጠ​ቅ​መ​ዋል።

9 ከግ​ፈ​ኞች ብዛት የተ​ነሣ ሰዎች ይጮ​ኻሉ፤ ከብ​ዙ​ዎች ክንድ የተ​ነ​ሣም ለር​ዳታ ይጠ​ራሉ።

10 ነገር ግን በሌ​ሊት ጥበ​ቃን የሚ​ያ​ዝዝ ፈጣ​ሪዬ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወዴት ነው? የሚል የለም፤

11 እር​ሱም ከም​ድር እን​ስ​ሶች ይልቅ፥ ከሰ​ማ​ይም ወፎች ይልቅ የሚ​ለ​የኝ ነው።

12 በዚያ ስለ ክፉ ሰዎች ስድብ ይጮ​ኻሉ፥ እርሱ ግን አይ​ሰ​ማ​ቸ​ውም።

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ው​ነት ክፉ ነገ​ርን ሊያይ አይ​ወ​ድም። እርሱ ሁሉን የሚ​ችል ዐዋቂ አም​ላክ ነውና።

14 ክፉ የሚ​ሠ​ሩ​ትን አይ​ሰ​ማ​ቸ​ውም፥ እኔ​ንም ያድ​ነ​ኛል፤ አንተ አሁን የሚ​ቻል እንደ መሆኑ መጠን ልታ​መ​ሰ​ግ​ነው ትችል እንደ ሆነ እስኪ በፊቱ ተዋ​ቀስ።

15 አሁን ቍጣ​ውን የሚ​ያ​ውቅ የለ​ምና፥ ታላቅ ኀጢ​አ​ቱ​ንም የሚ​ያ​ስብ የለ​ምና።

16 ኢዮብ ግን አፉን በከ​ንቱ ይከ​ፍ​ታል፥ ያለ ዕው​ቀ​ትም ቃሉን ያበ​ዛል።”

跟着我们:



广告