Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 31 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 “ከዐ​ይኔ ጋር ቃል ኪዳን አደ​ረ​ግሁ፥ ድን​ግ​ሊ​ቱ​ንም አል​ተ​መ​ለ​ከ​ት​ሁም፤

2 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እድል ፋንታ ከላይ፥ ሁሉ​ንም የሚ​ችል የአ​ም​ላክ ርስት ከአ​ር​ያም ምን​ድን ነው?

3 ሞት ለዐ​መ​ፀኛ፥ መለ​የ​ትም ኀጢ​አ​ትን ለሚ​ሠሩ ነው።

4 እርሱ መን​ገ​ዴን የሚ​ያይ አይ​ደ​ለ​ምን? እር​ም​ጃ​ዬ​ንስ ሁሉ የሚ​ቈ​ጥር አይ​ደ​ለ​ምን?

5 ከፌ​ዘ​ኞች ጋር ሄጄ እንደ ሆነ፥ እግ​ሬም ከመ​ን​ገዱ ገለል ብላ እንደ ሆነ፥

6 በእ​ው​ነ​ተኛ ሚዛን ልመ​ዘን፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቅን​ነ​ቴን ያው​ቃል።

7 እር​ም​ጃዬ ከመ​ን​ገዱ ፈቀቅ ብሎ እንደ ሆነ፥ ልቤም ዐይ​ኔን ተከ​ትሎ እንደ ሆነ፥ ጉቦም በእጄ ተጣ​ብቆ እንደ ሆነ፥

8 እኔ ልዝራ፥ ሌላ ሰውም ይብ​ላው፤ በም​ድር ላይ ሥሬ ይነ​ቀል።

9 ልቤ ወደ ሌላ ወንድ ሚስት ተከ​ትሎ እንደ ሆነ፥ በደ​ጅ​ዋም አድ​ብቼ እንደ ሆነ፥

10 ሚስቴ ሌላ​ውን ሰው ደስ ታሰኝ። ልጆ​ቼም ይዋ​ረዱ።

11 የሌ​ላ​ውን ወንድ ሚስት ማር​ከስ፥ የማ​ይ​ቈ​ጣ​ጠ​ሩት የቍጣ መቅ​ሠ​ፍት ነው።

12 ይህ በሕ​ዋ​ሳት ሁሉ የሚ​ነ​ድድ እሳት፥ የገ​ባ​በ​ት​ንም ሁሉ ከሥር የሚ​ነ​ቅል ነውና።

13 “ወንድ ባሪ​ያዬ ወይም ሴት ባሪ​ያዬ በእኔ ዘንድ በተ​ም​ዋ​ገቱ ጊዜ፥ ፍር​ዳ​ቸ​ውን አዳ​ልቼ እንደ ሆነ፥

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ረ​መ​ረኝ ጊዜ ምን አደ​ር​ጋ​ለሁ? በጐ​በ​ኘኝ ጊዜስ በፊቱ ምን እመ​ል​ስ​ለ​ታ​ለሁ?

15 እኔን በማ​ኅ​ፀን የፈ​ጠረ እነ​ር​ሱ​ንስ የፈ​ጠረ አይ​ደ​ለ​ምን? በማ​ኅ​ፀ​ንስ ውስጥ የሠ​ራን አንድ አይ​ደ​ለ​ምን?

16 “ድሆች የሚ​ሹ​ትን እን​ዳ​ያ​ገኙ አድ​ርጌ እንደ ሆነ፥ የመ​በ​ለ​ቲ​ቱ​ንም ዐይን አጨ​ልሜ እንደ ሆነ፥

17 እን​ጀ​ራ​ዬን ለብ​ቻዬ በልቼ እንደ ሆነ፥ ለድ​ሃ​አ​ደ​ጉም ደግሞ ከእ​ርሱ አላ​ካ​ፈ​ልሁ እንደ ሆነ፥

18 እር​ሱን ከታ​ና​ሽ​ነቱ ጀምሮ እንደ አባቱ ከእ​ኔው ጋር አሳ​ድ​ጌው ነበር፤ ከእ​ና​ቱም ማኅ​ፀን ከተ​ወ​ለደ ጀምሮ አሳ​ደ​ግ​ሁት።

19 ራቁ​ቱን የሆ​ነው ሰው በብ​ርድ ሲሞት አይቼ፥ አላ​ለ​በ​ስ​ሁት እንደ ሆነ፥

20 ድሆች አል​መ​ረ​ቁኝ እንደ ሆነ፥ በበ​ጎ​ቼም ጠጕር ትከ​ሻ​ቸው አል​ሞቀ እንደ ሆነ፥

21 ብዙ ረዳት እን​ዳ​ለኝ ተማ​ምኜ በድ​ሃ​አ​ደጉ ላይ እጄን አን​ሥቼ እንደ ሆነ፥

22 ትከ​ሻዬ ከመ​ሠ​ረቷ ትው​ደቅ፥ ክን​ዴም ከመ​ገ​ና​ኛዋ ትሰ​በር።

23 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግርማ አስ​ደ​ን​ግ​ጦ​ኛ​ልና፤ በእ​ር​ሱም ከመ​ያዝ በም​ክ​ን​ያት ማም​ለጥ አል​ቻ​ል​ሁም።

24 “ወር​ቄን በመ​ሬት ውስጥ ቀብሬ እንደ ሆነ፥ ዋጋው ብዙ በሆነ ዕንቍ ታም​ኜም እንደ ሆነ፥

25 ሀብቴ በበዛ ጊዜ፥ ደስ ብሎኝ እንደ ሆነ፥ ስፍር ቍጥር በሌ​ለ​ውም መዝ​ገብ ላይ እጄን ጨምሬ እንደ ሆነ፥

26 የሚ​ያ​በራ ፀሐይ እን​ደ​ሚ​ጠፋ ጨረ​ቃም እን​ደ​ም​ት​ጨ​ልም አላ​ይ​ምን? በራ​ሳ​ቸው ለመ​ኖር ኀይል የላ​ቸ​ው​ምና፥

27 ልቤ በስ​ውር ተታ​ልሎ እንደ ሆነ፥ በአ​ፌም ላይ እጄን አኑሬ ስሜ እንደ ሆነ፥

28 በል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በዋ​ሸሁ ነበ​ርና ይህ ደግሞ ትልቅ በደል ይሁ​ን​ብኝ።

29 በጠ​ላቴ ውድ​ቀት ደስ ብሎኝ እንደ ሆነ፥ በል​ቤም እሰይ ብዬ እንደ ሆነ፥

30 ጆሮዬ መር​ገ​ሜን ትስማ፤ በወ​ገ​ኔም መካ​ከል ክፉ ስም ይው​ጣ​ልኝ።

31 “ቤተ ሰቦቼ እኔ ስራ​ራ​ላ​ቸው፥ ሥጋ​ውን እን​በላ ዘንድ ማን በሰ​ጠን ብለው እንደ ሆነ፥

32 መጻ​ተ​ኛው ግን በሜዳ አያ​ድ​ርም ነበር፥ ደጄ​ንም ለመ​ጣው ሁሉ እከ​ፍት ነበር፤

33 ታላቅ በደ​ልም በድዬ እንደ ሆነ፥ ኀጢ​አ​ቴ​ንም ሰውሬ እንደ ሆነ፥

34 ከብዙ ሕዝብ የተ​ነሣ በፊ​ታ​ቸው ለመ​ና​ገር አፍሬ እንደ ሆነ፥ ድሃ​ውም ከደጄ ባዶ​ውን ወጥቶ እንደ ሆነ፥

35 የሚ​ያ​ደ​ም​ጠ​ኝን ማን በሰ​ጠኝ! የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም እጅ አል​ፈ​ራሁ እንደ ሆነ፥ የሚ​ያ​ስ​ፈ​ር​ድ​ብኝ የክስ ጽሑፍ ምነው በኖ​ረኝ!

36 በት​ከ​ሻዬ ላይ እሸ​ከ​መው ነበር፥ አክ​ሊ​ልም አድ​ርጌ በራሴ አስ​ረው ነበር፥ በብ​ዙ​ዎ​ችም መካ​ከል አነ​ብ​በው ነበር፤

37 ከባለ ዕዳዬ የም​ቀ​በ​ለው ሳይ​ኖር ቀድ​ጀው እመ​ለ​ሳ​ለሁ።

38 “እር​ሻዬ በእኔ ላይ ጮኻ እንደ ሆነ፥ ትል​ሞ​ች​ዋም በአ​ንድ ላይ አል​ቅ​ሰው እንደ ሆነ፥

39 ፍሬ​ዋን ለብ​ቻዬ ያለ ዋጋ በልቼ እንደ ሆነ፥ ባለ መሬ​ቱ​ንም አባ​ርሬ ነፍ​ሱን አሳ​ዝኜ እንደ ሆነ፥

40 በስ​ንዴ ፋንታ እን​ክ​ር​ዳድ፥ በገ​ብ​ስም ፋንታ ኵር​ን​ችት ይብ​ቀ​ል​ብኝ።” ኢዮ​ብም ነገ​ሩን ፈጸመ።

跟着我们:



广告