Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 28 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 “በእ​ው​ነቱ ብር የሚ​ወ​ጣ​በት ቦታ አለ፥ ወር​ቅም የሚ​ነ​ጠ​ር​በት ስፍራ አለ።

2 ብረ​ትም ከመ​ሬት ውስጥ ይወ​ጣል፤ መዳ​ብም እንደ ድን​ጋይ ይፈ​ለ​ጣል።

3 ለጨ​ለማ ወሰ​ንን ያደ​ር​ጋል፤ እርሱ ሁሉን ይመ​ረ​ም​ራል፥ የጨ​ለ​ማ​ንና የሞት ጥላ ድን​ጋ​ይ​ንም ይመ​ረ​ም​ራል።

4 በአ​ፈር ምክ​ን​ያት እን​ደ​ሚ​ከ​ፈል ወንዝ የጽ​ድ​ቅን መን​ገድ የረሱ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ይደ​ክ​ማሉ። ከሰ​ዎ​ችም መካ​ከል ይለ​ያሉ።

5 እን​ጀራ ከም​ድር ውስጥ ይወ​ጣል፤ በእ​ሳ​ትም እን​ደ​ሚ​ሆን ታች​ኛው ይገ​ለ​በ​ጣል።

6 ድን​ጋ​ይዋ እንደ ሰን​ፔር፥ ወር​ቅ​ዋም እንደ አፈር የሆነ መሬት አለች።

7 መን​ገ​ድ​ዋን ዎፍ አያ​ው​ቀ​ውም፥ የን​ስ​ርም ዐይን አላ​የ​ውም።

8 የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ልጆች አል​ረ​ገ​ጡ​አ​ትም፥ ደቦል አን​በ​ሳም በው​ስ​ጥዋ አላ​ለ​ፈ​ባ​ትም።

9 ሰው ወደ ቡላድ ድን​ጋይ እጁን ይዘ​ረ​ጋል፥ ተራ​ራ​ዎ​ች​ንም ከመ​ሠ​ረ​ታ​ቸው ይገ​ለ​ብ​ጣ​ቸ​ዋል።

10 ከድ​ን​ጋይ ውስጥ መን​ዶ​ል​ዶያ ይወ​ቅ​ራል፤ ዐይ​ኔም የከ​በ​ረ​ውን ነገር ሁሉ ታያ​ለች።

11 የፈ​ሳ​ሹ​ንም ጥል​ቀት ይገ​ል​ጣል። ኀይ​ሉ​ንም በብ​ር​ሃን ይገ​ል​ጣል።

12 “ነገር ግን ጥበብ ወዴት ትገ​ኛ​ለች? የጥ​በ​ብስ ሀገ​ርዋ ወዴት ነው?

13 ሟች ሰው መን​ገ​ድ​ዋን አያ​ው​ቅም፤ በሰ​ዎ​ችም ዘንድ አት​ገ​ኝም።

14 ቀላይ፦ በእኔ ውስጥ የለ​ችም ትላ​ለች። ባሕ​ርም፦ በእኔ ዘንድ የለ​ችም ይላል።

15 ስለ እር​ስ​ዋም ማንም ምዝ​ምዝ ወርቅ አይ​ሰ​ጥም ብርም በእ​ር​ስዋ ለውጥ አይ​መ​ዘ​ንም።

16 ከአ​ፌር ወር​ቅም ጋር አት​ወ​ዳ​ደ​ርም። በከ​በረ መረ​ግ​ድና በሰ​ን​ፔር አት​ገ​መ​ትም።

17 ወር​ቅና ብር​ጭቆ አይ​ወ​ዳ​ደ​ሩ​አ​ትም፥ የወ​ር​ቅም ጥሬ ዕቃ የእ​ር​ስዋ ለውጥ አይ​ሆ​ንም።

18 ዛጎ​ልና አል​ማዝ አይ​ታ​ሰ​ቡም። አንተ ግን እጅግ ከከ​በሩ ነገ​ሮች ሁሉ ይልቅ ጥበ​ብን አቅ​ር​ባት።

19 የኢ​ት​ዮ​ጵያ ሉል አይ​ተ​ካ​ከ​ላ​ትም፥ በጥ​ሩም ወርቅ አት​ገ​መ​ትም።

20 “እን​ግ​ዲያ ጥበብ ከወ​ዴት ትገ​ኛ​ለች? የማ​ስ​ተ​ዋ​ልስ ሀገሯ ወዴት ነው?

21 በሰው ሁሉ ዘንድ ተረ​ስ​ታ​ለች፥ ከሰ​ማይ ወፎ​ችም ተሰ​ው​ራ​ለች።

22 ሞትና ሲኦል ወሬ​ዋን በጆ​ሮ​ቻ​ችን ሰማን ብለ​ዋል።

23 “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገ​ድ​ዋን አሳ​መረ፥ እር​ሱም ስፍ​ራ​ዋን ያው​ቃል።

24 እር​ሱም በሰ​ማይ ያለ​ውን ይመ​ለ​ከ​ታል፥ በም​ድ​ርም ያለ​ውን ሁሉ ያው​ቃል።

25 ለነ​ፋስ ሚዛ​ንን ለው​ሆ​ችም መስ​ፈ​ሪ​ያን አደ​ረገ።

26 እነ​ዚ​ህን በፈ​ጠረ ጊዜ እን​ዲሁ ዐውቆ ቈጠ​ራ​ቸው። ለዝ​ናም ሥር​ዐ​ትን ለነ​ጐ​ድ​ጓድ መብ​ረ​ቅም መን​ገ​ድን አደ​ረገ።

27 በዚ​ያን ጊዜ አያት፥ ገለ​ጣ​ትም፤ አዘ​ጋ​ጃ​ትም፥ አከ​በ​ራት፥ ደግ​ሞም መረ​መ​ራት።

28 ሰው​ንም፦ ‘እነሆ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ጥበብ ነው፤ ከክፉ መራ​ቅም ማስ​ተ​ዋል ነው’ ” አለው።

跟着我们:



广告