Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ሕዝቅኤል 30 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ጌታ ግብ​ፅን እን​ደ​ሚ​ቀጣ

1 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ወደ እኔ እን​ዲህ ሲል መጣ፦

2 “የሰው ልጅ ሆይ! ትን​ቢት ተና​ገር፤ እን​ዲ​ህም በል፦ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ዋይ! በሉ፥ ለቀኑ ወዮ!

3 ቀኑ ቅርብ ነው፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀን ቅርብ ነው፤ የደ​መና ቀን፥ የአ​ሕ​ዛብ ማለ​ቂያ ጊዜ ይሆ​ናል።

4 ሰይፍ በግ​ብፅ ላይ ይመ​ጣል፤ ሁከ​ትም በኢ​ት​ዮ​ጵያ ይሆ​ናል፤ የተ​ገ​ደ​ሉ​ትም በግ​ብፅ ውስጥ ይወ​ድ​ቃሉ፤ ብዛ​ቷ​ንም ይወ​ስ​ዳሉ፤ መሠ​ረ​ቷም ይፈ​ር​ሳል።

5 ኢት​ዮ​ጵ​ያና ፉጥ፥ ሉድም፥ ዓረ​ብም ሁሉ፥ ኩብም፤ ሊብ​ያም፤ ቀር​ጤ​ስም የተ​ደ​ባ​ለቀ ሕዝ​ብም ሁሉ፥ ቃል ኪዳ​ን​ንም የገ​ባ​ችው ምድር ልጆች ከእ​ነ​ርሱ ጋር በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃሉ።

6 “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ ይላል፦ ግብ​ፅን የሚ​ደ​ግፉ ይወ​ድ​ቃሉ፤ የኀ​ይ​ል​ዋም ትዕ​ቢት ይወ​ር​ዳል፤ ከሚ​ግ​ዶል ጀምሮ እስከ ሰዌኔ ድረስ በእ​ር​ስዋ ውስጥ በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃሉ፥ ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።

7 ባድ​ማም በሆኑ ሀገ​ሮች መካ​ከል ባድማ ይሆ​ናሉ፤ ከተ​ሞ​ች​ዋም በፈ​ረሱ ከተ​ሞች መካ​ከል ይሆ​ናሉ።

8 እሳ​ት​ንም በግ​ብፅ ላይ በአ​ነ​ደ​ድሁ ጊዜ፥ ረዳ​ቶ​ች​ዋም ሁሉ በተ​ሰ​በሩ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።

9 በዚያ ቀን መል​እ​ክ​ተ​ኞች ተዘ​ል​ለው የሚ​ኖ​ሩ​ትን ኢት​ዮ​ጵ​ያ​ው​ያ​ንን ለማ​ጥ​ፋት ከፊቴ በመ​ር​ከብ ይወ​ጣሉ፤ በግ​ብ​ፅም ቀን ሁከት ይሆ​ን​ባ​ቸ​ዋል፤ እነሆ፥ ይመ​ጣ​ልና።

10 “ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የግ​ብ​ፅን ብዛት በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር እጅ አጠ​ፋ​ለሁ።

11 እር​ሱና ሕዝቡ የአ​ሕ​ዛ​ብም ኀያ​ላን ምድ​ሪ​ቱን ለማ​ጥ​ፋት ይላ​ካሉ፤ ግብ​ፃ​ው​ያ​ን​ንም በሰ​ይፍ ይወ​ጉ​አ​ቸ​ዋል፤ ምድ​ሪ​ቱም በሙ​ታን ትሞ​ላ​ለች።

12 ወን​ዞ​ች​ንም ምድረ በዳ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ ምድ​ሪ​ቱ​ንም በክፉ ሰዎች እጅ እሰ​ጣ​ለሁ፥ ምድ​ሪ​ቱ​ንና ሞላ​ዋ​ንም በባ​ዕ​ዳን እጅ ባድማ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተና​ግ​ሬ​አ​ለሁ።

13 “ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ጣዖ​ቶ​ቹን አጠ​ፋ​ለሁ፤ ምስ​ሎ​ቹ​ንም ከሜ​ም​ፎስ እሽ​ራ​ለሁ፤ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲ​ያም በግ​ብፅ ምድር አለቃ አይ​ሆ​ንም፤ በግ​ብፅ ምድር ላይም ፍር​ሀ​ትን አደ​ር​ጋ​ለሁ።

14 ጳት​ሮ​ስ​ንም አፈ​ር​ሳ​ለሁ፤ በጣ​ኔ​ዎ​ስም ላይ እሳ​ትን አነ​ድ​ዳ​ለሁ፤ በዲ​ዮ​ስ​ጶ​ሊን ላይም ፍር​ድን አደ​ር​ጋ​ለሁ።

15 በግ​ብ​ፅም ኀይል በሲን ላይ መዓ​ቴን አፈ​ስ​ሳ​ለሁ፤ የሜ​ም​ፎ​ስ​ንም ብዛት አጠ​ፋ​ለሁ።

16 በግ​ብ​ፅም ላይ እሳ​ትን አነ​ድ​ዳ​ለሁ፤ ሲንም ትታ​ወ​ካ​ለች፤ ኖእም ትሰ​በ​ራ​ለች፤ ሜም​ፎ​ስም ምድረ በዳ ትሆ​ና​ለች።

17 የሄ​ል​ዮቱ ከተ​ማና የቡ​ባ​ስ​ቱም ጐል​ማ​ሶች በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃሉ፤ ሴቶ​ችም ይማ​ረ​ካሉ።

18 የግ​ብ​ፅን ቀን​በር በዚያ በሰ​በ​ርሁ ጊዜ በጣ​ፍ​ናስ ቀኑ ይጨ​ል​ማል፤ የኀ​ይ​ል​ዋም ትዕ​ቢት ይጠ​ፋ​ባ​ታል፤ ደመ​ናም ይጋ​ር​ዳ​ታል፤ ሴቶች ልጆ​ች​ዋም ይማ​ረ​ካሉ።

19 እን​ዲሁ በግ​ብፅ ላይ ፍር​ድን አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”

20 እን​ዲ​ህም ሆነ፤ በዐ​ሥራ አን​ደ​ኛው ዓመት በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር ከወ​ሩም በሰ​ባ​ተ​ኛው ቀን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ወደ እኔ እን​ዲህ ሲል መጣ፦

21 “የሰው ልጅ ሆይ! የግ​ብ​ፅን ንጉሥ የፈ​ር​ዖ​ንን ክንድ ሰብ​ሬ​አ​ለሁ፥ እነ​ሆም ይድን ዘንድ መድ​ኃ​ኒት ቀብ​ተው አያ​ደ​ር​ቁ​ትም፤ ሰይ​ፉ​ንም ለመ​ያዝ ኀይ​ልን ያገኝ ዘንድ አል​ታ​ሰ​ረም።

22 ስለ​ዚህ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እነሆ እኔ በግ​ብፅ ንጉሥ በፈ​ር​ዖን ላይ ነኝ የጸ​ና​ች​ው​ንና የተ​ሰ​በ​ረ​ች​ው​ንም ክን​ዱን እሰ​ብ​ራ​ለሁ፤ ሰይ​ፉ​ንም ከእጁ አስ​ጥ​ለ​ዋ​ለሁ።

23 ግብ​ፃ​ው​ያ​ን​ንም በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል እበ​ት​ና​ለሁ፤ በሀ​ገ​ሮ​ችም መካ​ከል እዘ​ራ​ቸ​ዋ​ለሁ።

24 የባ​ቢ​ሎ​ን​ንም ንጉሥ ክንድ አበ​ረ​ታ​ለሁ፤ ሰይ​ፌ​ንም በእጁ እሰ​ጣ​ለሁ፤ ግብ​ፅ​ንም ይወ​ጋ​በ​ታል፥ ምር​ኮ​ዋ​ንም ይማ​ር​ካል፤ ሰለ​ባ​ዋ​ንም ይሰ​ል​ባል።

25 የባ​ቢ​ሎ​ን​ንም ንጉሥ ክንድ አጸ​ና​ለሁ፤ የፈ​ር​ዖ​ንም ክንድ ይወ​ድ​ቃል፤ ሰይ​ፌ​ንም በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ እጅ በሰ​ጠሁ ጊዜ፥ እር​ሱም በግ​ብፅ ምድር ላይ በዘ​ረ​ጋው ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።

26 ግብ​ፃ​ው​ያ​ን​ንም በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል እበ​ት​ና​ለሁ፤ በሀ​ገ​ሮ​ችም መካ​ከል እዘ​ራ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ሁሉም እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”

跟着我们:



广告