Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ሕዝቅኤል 23 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሁለት አመ​ን​ዝራ እኅ​ት​ማ​ማ​ቾች

1 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ወደ እኔ እን​ዲህ ሲል መጣ፦

2 “የሰው ልጅ ሆይ፥ የአ​ን​ዲት እናት ልጆች የሆኑ ሁለት ሴቶች ነበሩ።

3 በግ​ብፅ ሀገር አመ​ነ​ዘሩ፤ በኮ​ረ​ዳ​ነ​ታ​ቸው ሳሉ አመ​ነ​ዘሩ፤ በዚ​ያም ጡቶ​ቻ​ቸው ወደቁ፤ በዚ​ያም ድን​ግ​ል​ና​ቸ​ውን አጡ።

4 ስማ​ቸ​ውም የታ​ላ​ቂቱ ሐላ የታ​ናሽ እኅ​ቷም ሐሊባ ነበረ፤ እኔም አገ​ባ​ኋ​ቸው፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ች​ንም ወለዱ። ስማ​ቸ​ውም ሐላ ሰማ​ርያ ናት፤ ሐሊባ ደግሞ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ናት።

5 “ሐላም አመ​ነ​ዘ​ረ​ች​ብኝ፤ ወዳ​ጆ​ች​ዋ​ንም የሚ​ቀ​ር​ቡ​አ​ትን አሦ​ራ​ው​ያ​ንን በፍ​ቅር ተከ​ተ​ለ​ቻ​ቸው።

6 እነ​ር​ሱም ሰማ​ያዊ ሐር የለ​በሱ መሳ​ፍ​ን​ትና መኳ​ን​ንት፥ መልከ መል​ካ​ሞች ጐበ​ዛ​ዝት፥ በፈ​ረስ ላይ የሚ​ቀ​መጡ የተ​መ​ረጡ ፈረ​ሰ​ኞች ነበሩ።

7 ዝሙ​ቷ​ንም ከተ​መ​ረጡ ከአ​ሦር ሰዎች ሁሉ ጋር አደ​ረ​ገች፤ በፍ​ቅር በተ​ከ​ተ​ለ​ቻ​ቸ​ውም ጣዖ​ቶ​ቻ​ቸው ሁሉ ረከ​ሰች።

8 በግ​ብ​ፅም የነ​በ​ረ​ውን ዝሙ​ቷን አል​ተ​ወ​ችም፤ በዚ​ያም በኮ​ረ​ዳ​ነቷ ጊዜ ከእ​ር​ስዋ ጋር ተኝ​ተው ነበር፤ የድ​ን​ግ​ል​ና​ዋ​ንም ጡቶች ዳብ​ሰው ነበር፤ ዝን​የ​ታ​ቸ​ው​ንም አፍ​ስ​ሰ​ው​ባት ነበር።

9 ስለ​ዚህ በፍ​ቅር በተ​ከ​ተ​ለ​ቻ​ቸው በወ​ዳ​ጆ​ችዋ በአ​ሦ​ራ​ው​ያን እጆች አሳ​ልፌ ሰጠ​ኋት።

10 እነ​ር​ሱም ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን ገለጡ፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ች​ዋ​ንም ማር​ከው ወሰዱ፤ እር​ስ​ዋ​ንም በሰ​ይፍ ገደሉ፤ በእ​ር​ስ​ዋና በሴ​ቶች ልጆ​ችዋ ላይ በቀ​ልን ስላ​ደ​ረ​ጉ​ባ​ቸው በሴ​ቶች መካ​ከል መተ​ረቻ ሆነች።

11 “እኅ​ቷም ሐሊባ ይህን አየች፤ ሆኖም ከእ​ር​ስዋ ይልቅ በፍ​ቅር በመ​ከ​ተ​ልዋ ረከ​ሰች፤ ዝሙ​ቷ​ንም ከእ​ኅቷ ዝሙት ይልቅ አበ​ዛች።

12 የሚ​ቀ​ር​ቡ​አ​ትን መሳ​ፍ​ን​ቱ​ንና መኳ​ን​ን​ቱን ጌጠኛ ልብስ የለ​በ​ሱ​ትን፥ በፈ​ረ​ሶች ላይ የሚ​ቀ​መ​ጡ​ትን ፈረ​ሰ​ኞች፥ ሁሉ​ንም መልከ መል​ካ​ሞ​ችን ጐበ​ዛ​ዝት አሦ​ራ​ው​ያ​ንን በፍ​ቅር ተከ​ተ​ለ​ቻ​ቸው።

13 እንደ ረከ​ሱም አየሁ፤ ሁለ​ቱም አንድ መን​ገድ ሄደ​ዋል።

14 ዳግ​መ​ኛም ዝሙ​ቷን አበ​ዛች፤ በግ​ንብ ላይ የተ​ሣሉ የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሰዎች ሥዕ​ል​ንም አየሁ።

15 በጥ​ቍር ቀለም የተ​ሣሉ የከ​ለ​ዳ​ው​ያ​ንን መልክ አየሁ፤ በወ​ገ​ባ​ቸው ዝናር የታ​ጠቁ ናቸው፤ በራ​ሳ​ቸ​ውም ላይ ጥልፍ ሰበን የጠ​መ​ጠሙ ናቸው፤ ፊታ​ቸ​ውም ሦስት ወገን ነው፤ ሁሉም በት​ው​ልድ ሀገ​ራ​ቸው የሚ​ኖሩ የባ​ቢ​ሎን ሰዎ​ችን ከለ​ዳ​ው​ያ​ንን ይመ​ስ​ላሉ።

16 ዐይ​ን​ዋ​ንም ወደ እነ​ርሱ አቅ​ንታ አየ​ቻ​ቸው፤ ወደ ከላ​ው​ዴ​ዎ​ንም ምድር ወደ እነ​ርሱ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላከች።

17 የባ​ቢ​ሎ​ንም ልጆች ወደ እር​ስዋ መጥ​ተው በመ​ኝ​ታዋ ከእ​ር​ስዋ ጋር ተኙ፤ በዝ​ሙ​ታ​ቸ​ውም አረ​ከ​ሱ​አት፤ እር​ስ​ዋም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ረከ​ሰች፤ ነፍ​ስ​ዋም ከእ​ነ​ርሱ ተለ​የች።

18 ዝሙ​ቷ​ንም ገለ​ጠች፤ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋ​ንም ገለ​ጠች፤ ነፍ​ሴም ከእ​ኅቷ እንደ ተለ​የች እን​ዲሁ ነፍሴ ከእ​ር​ስዋ ተለ​የች።

19 ነገር ግን በግ​ብፅ ምድር ያመ​ነ​ዘ​ረ​ሽ​በ​ትን የወ​ጣ​ት​ነ​ት​ሽን ዘመን አስ​በሽ ዝሙ​ት​ሽን አበ​ዛሽ።

20 አካ​ላ​ቸ​ውም እንደ አህ​ዮች አካል፤ ዘራ​ቸ​ውም እንደ ፈረ​ሶች ዘር የሆ​ነ​ውን እነ​ዚ​ያን የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ልጆች በፍ​ቅር ተከ​ተ​ል​ሻ​ቸው።

21 ጡትሽ በአ​ጐ​ጠ​ጐጠ ጊዜ በማ​ደ​ሪ​ያሽ በግ​ብፅ ሀገር የሠ​ራ​ሽ​ውን የወ​ጣ​ት​ነ​ት​ሽን ኀጢ​አት አሰ​ብሽ።”

22 ስለ​ዚህ ሐሊባ ሆይ! ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ነፍ​ስሽ ከእ​ነ​ርሱ የተ​ለ​የች ወዳ​ጆ​ች​ሽን አስ​ነ​ሣ​ብ​ሻ​ለሁ፤ በዙ​ሪ​ያ​ሽም በአ​ንቺ ላይ አመ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ።

23 እነ​ር​ሱም የባ​ቢ​ሎን ልጆች፥ ከለ​ዳ​ው​ያ​ንም ሁሉ፥ ፋቁድ፥ ሱሔ፥ ቆዓ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር አሦ​ራ​ው​ያን ሁሉ፥ መልከ መል​ካ​ሞች ጐበ​ዛ​ዝት፥ መሳ​ፍ​ን​ትና መኳ​ን​ንት ሁሉ፥ መሳ​ፍ​ን​ትና አማ​ካ​ሪ​ዎች ሁሉ፥ በሦ​ስት ወገን በፈ​ረስ ላይ የተ​ቀ​መጡ ናቸው።

24 ስማ​ቸ​ውን ያስ​ጠሩ ሰዎች ሁሉ በመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ርና በሠ​ረ​ገላ፥ በአ​ሕ​ዛ​ብም ጉባኤ ይመ​ጡ​ብ​ሻል፤ ጋሻና አላ​ባሽ ጋሻ፥ ራስ ቍርም ይዘው በዙ​ሪ​ያሽ ጥበቃ ያደ​ር​ጋሉ፤ ፍር​ድ​ንም እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እንደ ፍር​ዳ​ቸ​ውም ይፈ​ር​ዱ​ብ​ሻል።

25 ቅን​አ​ቴ​ንም በአ​ንቺ ላይ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ በመ​ዓ​ትም ያደ​ር​ጉ​ብ​ሻል፤ አፍ​ን​ጫ​ሽ​ንና ጆሮ​ሽ​ንም ከአ​ንቺ ይቈ​ር​ጣሉ፤ ከአ​ን​ቺም የቀረ በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃል፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ች​ሽ​ንም ማር​ከው ይወ​ስ​ዳሉ፤ ከአ​ን​ቺም የቀ​ሩ​ትን እሳት ትበ​ላ​ቸ​ዋ​ለች።

26 ልብ​ስ​ሽ​ንም ይገ​ፍ​ፉ​ሻል፤ የክ​ብ​ር​ሽ​ንም ጌጥ ይወ​ስ​ዳሉ።

27 ሴሰ​ኝ​ነ​ት​ሽ​ንም፥ ከግ​ብፅ ምድር ያወ​ጣ​ሽ​ውን ዝሙ​ት​ሽ​ንም ከአ​ንቺ አስ​ቀ​ራ​ለሁ፤ ዐይ​ን​ሽ​ንም ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ ወደ እነ​ርሱ አታ​ነ​ሺም፤ ግብ​ፅ​ንም ከዚያ ወዲያ አታ​ስ​ቢም።

28 ስለ​ዚህ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እነሆ በጠ​ላ​ሻ​ቸው እጅ፥ ነፍ​ስ​ሽም በተ​ለ​የ​ቻ​ቸው እጅ አሳ​ልፌ እሰ​ጥ​ሻ​ለሁ፤

29 እነ​ር​ሱም በጥል ያደ​ር​ጉ​ብ​ሻል፤ የደ​ከ​ም​ሽ​በ​ት​ንም ሁሉ ይወ​ስ​ዳሉ፤ ዕራ​ቁ​ት​ሽ​ንና ዕር​ቃ​ን​ሽን አድ​ር​ገ​ውም ይተ​ዉ​ሻል፤ የግ​ል​ሙ​ት​ና​ሽ​ንም ነውር፥ ሴሰ​ኝ​ነ​ት​ሽ​ንና ግል​ሙ​ት​ና​ሽ​ንም ሁሉ ይገ​ል​ጣሉ።

30 ከአ​ሕ​ዝብ ጋር ስላ​መ​ነ​ዘ​ርሽ፤ በበ​ደ​ላ​ቸ​ውም ስለ ረከ​ስሽ ይህን ያደ​ር​ጉ​ብ​ሻል።

31 በእ​ኅ​ትሽ መን​ገድ ሄደ​ሻል፤ ስለ​ዚህ ጽዋ​ዋን በእ​ጅሽ እሰ​ጥ​ሻ​ለሁ።

32 ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የጠ​ለ​ቀ​ው​ንና የሰ​ፋ​ውን፥ ብዙም የሚ​ይ​ዘ​ውን የእ​ኅ​ት​ሽን ጽዋ ትጠ​ጪ​አ​ለሽ፤ ብዙ መጠ​ጥን በሚ​ጠጡ ሰዎ​ችም ዘንድ መሳ​ቂ​ያና መሳ​ለ​ቂያ ትሆ​ኛ​ለሽ።

33 በእ​ኅ​ትሽ በሰ​ማ​ርያ ጽዋ፥ በድ​ን​ጋ​ጤና በጥ​ፋት ጽዋ፥ በስ​ካ​ርና በው​ር​ደት ትሞ​ሊ​ያ​ለሽ።

34 ትጠ​ጪ​ዋ​ለሽ፥ ትጨ​ል​ጪ​ው​ማ​ለሽ፤ በዓ​ላ​ት​ሽ​ንና መባ​ቻ​ዎ​ች​ሽን እሽ​ራ​ለሁ፤ እኔ ተና​ግ​ሬ​አ​ለ​ሁና ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።

35 ስለ​ዚህ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ዘን​ግ​ተ​ሽ​ኛ​ልና፥ ወደ ኋላ​ሽም ጥለ​ሽ​ኛ​ልና አንቺ ደግሞ ሴሰ​ኝ​ነ​ት​ሽ​ንና ኀጢ​አ​ት​ሽን ተሸ​ከሚ።”

36 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ አለኝ፥ “የሰው ልጅ ሆይ! ሐላ​ንና ሐሊ​ባን ተፋ​ረ​ዳ​ቸው፤ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም አስ​ታ​ው​ቃ​ቸው፤

37 አመ​ን​ዝ​ረ​ዋ​ልና፥ ደምም በእ​ጃ​ቸው አለና፥ ዝሙ​ታ​ቸ​ው​ንም ወድ​ደ​ዋ​ልና፥ ለእ​ኔም የወ​ለ​ዱ​አ​ቸ​ውን ልጆ​ቻ​ቸ​ውን መብል እን​ዲ​ሆ​ኑ​ላ​ቸው በእ​ሳት አሳ​ል​ፈ​ዋ​ቸ​ዋ​ልና።

38 ይህን ደግሞ አድ​ር​ገ​ው​ብ​ኛል፤ በዚያ ቀን መቅ​ደ​ሴን አር​ክ​ሰ​ዋል፤ ሰን​በ​ታ​ቴ​ንም ሽረ​ዋል።

39 ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው በሠዉ ጊዜ ፥ በዚ​ያው ቀን ያረ​ክ​ሱት ዘንድ ወደ መቅ​ደሴ ገቡ፤ እነ​ሆም በቤቴ ውስጥ እን​ደ​ዚህ አደ​ረጉ።

40 ከሩቅ ሀገ​ርም ወደ​መጡ ሰዎች መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላኩ፤ እነ​ር​ሱም በደ​ረሱ ጊዜ ይታ​ጠ​ባሉ፤ ዐይ​ኖ​ቻ​ቸ​ው​ንም ይኳ​ላሉ፤ ያጌ​ጣ​ሉም።

41 በክ​ብር አልጋ ላይ ይቀ​መ​ጣሉ፤ በፊት ለፊ​ታ​ቸ​ውም ማዕድ ተዘ​ጋ​ጅታ ነበር፤ በዕ​ጣ​ኔና በዘ​ይ​ቴም ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

42 የበ​ገ​ና​ውን አው​ታር ድምፅ ይቃ​ኛሉ፤ ከብዙ ሰዎ​ችም ጉባኤ ጋር ሰካ​ራ​ሞቹ ከም​ድረ በዳ መጡ፤ በእ​ጃ​ቸው አን​ባር፥ በራ​ሳ​ቸ​ውም የተ​ዋበ አክ​ሊል አደ​ረጉ።

43 እኔም፦ ‘አሁን ከእ​ር​ስዋ ጋር ያመ​ነ​ዝ​ራሉ፤ እር​ስ​ዋም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ታመ​ነ​ዝ​ራ​ለች፤’ አልሁ።

44 ወደ ጋለ​ሞታ እን​ደ​ሚ​ገ​ቡም ወደ እር​ስዋ ገቡ፤ እን​ዲሁ ይሰ​ስኑ ዘንድ ወደ ሐላና ወደ ሐሊባ ገቡ።

45 ሴቶቹ አመ​ን​ዝ​ሮች ናቸ​ውና፥ በእ​ጃ​ቸ​ውም ደም አለና ጻድ​ቃን ሰዎች በአ​መ​ን​ዝ​ሮ​ቹና በደም አፍ​ሳ​ሾቹ ሴቶች ላይ በሚ​ፈ​ረ​ደው ፍርድ ይፈ​ር​ዱ​ባ​ቸ​ዋል።”

46 ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ጉባ​ኤን አመ​ጣ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ለመ​በ​ተ​ንና ለመ​በ​ዝ​በ​ዝም አሳ​ልፌ እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ።

47 ጉባ​ኤ​ውም በድ​ን​ጋይ ይወ​ግ​ሩ​አ​ቸ​ዋል፤ በሰ​ይ​ፋ​ቸ​ውም ይቈ​ር​ጡ​አ​ቸ​ዋል፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ይገ​ድ​ላሉ፤ ቤቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በእ​ሳት ያቃ​ጥ​ላሉ።

48 ሴቶ​ችም ሁሉ እንደ ኀጢ​አ​ታ​ችሁ እን​ዳ​ይ​ሠሩ ይማሩ ዘንድ ሴሰ​ኝ​ነ​ትን ከም​ድር ላይ አጠ​ፋ​ለሁ።

49 እን​ግ​ዲህ በደ​ላ​ችሁ በላ​ያ​ችሁ ላይ ይመ​ለ​ሳል፤ እና​ን​ተም የጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ች​ሁን ኀጢ​አት ትሸ​ከ​ማ​ላ​ችሁ፤ እኔም ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።”

跟着我们:



广告