Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

2 ዜና መዋዕል 33 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የይ​ሁዳ ንጉሥ የም​ናሴ ዘመነ መን​ግ​ሥት
( 2ነገ. 21፥1-9 )

1 ምና​ሴም መን​ገሥ በጀ​መረ ጊዜ የዐ​ሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም አምሳ አም​ስት ዓመት ነገሠ።

2 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት እን​ዳ​ወ​ጣ​ቸው እንደ አሕ​ዛብ ያለ ርኵ​ሰት በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ ነገ​ርን አደ​ረገ።

3 አባ​ቱም ሕዝ​ቅ​ያስ ያፈ​ረ​ሳ​ቸ​ውን የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎች መልሶ ሠራ፤ ለበ​ዓ​ሊ​ምም መሠ​ዊያ ሠራ፤ የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዶ​ች​ንም ተከለ፤ ለሰ​ማ​ይም ሠራ​ዊት ሁሉ ሰገደ፤ አመ​ለ​ካ​ቸ​ውም።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “ስሜ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል” ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት የጣ​ዖት መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ችን ሠራ።

5 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት በሁ​ለቱ አደ​ባ​ባ​ዮች ላይ ለሰ​ማይ ሠራ​ዊት ሁሉ መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ችን ሠራ።

6 በሄ​ኖ​ምም ልጅ ሸለቆ ውስጥ ልጆ​ቹን በእ​ሳት አቃ​ጠለ፤ ሞራ ገላ​ጭም ሆነ፤ አስ​ማ​ትም አደ​ረገ። መተ​ተ​ኛም ነበረ፤ መና​ፍ​ስት ጠሪ​ዎ​ች​ንና ጠን​ቋ​ዮ​ች​ንም ሰበ​ሰበ፤ ያስ​ቈ​ጣ​ውም ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እጅግ ክፉ ነገ​ርን አደ​ረገ።

7 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለዳ​ዊ​ትና ለልጁ ለሰ​ሎ​ሞን፥ “በዚህ ቤትና ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ ሁሉ በመ​ረ​ጥ​ኋት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ስሜን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አኖ​ራ​ለሁ፤

8 ያዘ​ዝ​ኋ​ቸ​ው​ንም ሁሉ፥ በሙሴ የተ​ሰ​ጠ​ውን ሕግና ሥር​ዐት ፍር​ድ​ንም ሁሉ ቢያ​ደ​ርጉ ቢጠ​ብ​ቁም፥ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ ከሰ​ጠ​ኋት ምድር የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን እግር እንደ ገና አላ​ር​ቅም” ባለ​በት በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ውስጥ የሠ​ራ​ውን ጣዖ​ትና የተ​ቀ​ረ​ጸ​ውን ምስል አቆመ።

9 ምና​ሴም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት ካጠ​ፋ​ቸው ከአ​ሕ​ዛብ ይልቅ ክፉ ይሠሩ ዘንድ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖ​ሩ​ትን አሳተ።

10 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ምና​ሴ​ንና ሕዝ​ቡን ተና​ገ​ራ​ቸው፤ ግን አል​ሰ​ሙ​ትም።

11 ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ሠራ​ዊት አለ​ቆች አመ​ጣ​ባ​ቸው፤ ምና​ሴ​ንም በዛ​ን​ጅር ያዙት፤ በሰ​ን​ሰ​ለ​ትም አስ​ረው ወደ ባቢ​ሎን ወሰ​ዱት።

12 በተ​ጨ​ነ​ቀም ጊዜ አም​ላ​ኩን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈለገ፤ በአ​ባ​ቶ​ቹም አም​ላክ ፊት ሰው​ነ​ቱን እጅግ አዋ​ረደ።

13 የን​ጉሡ የሕ​ዝ​ቅ​ያስ ልጅ ምና​ሴም ጸለየ እን​ዲ​ህም አለ፦


የም​ናሴ ጸሎት

14 “ዓለ​ምን ሁሉ የም​ት​ገዛ፥ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን የአ​ብ​ር​ሃ​ምና የይ​ስ​ሐቅ፥ የያ​ዕ​ቆ​ብም የጻ​ድ​ቃን ልጆ​ቻ​ቸ​ውም አም​ላክ ሆይ፥ ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን ከዓ​ለ​ሞ​ቻ​ቸው ጋር የፈ​ጠ​ርህ፥

15 በቃ​ልህ ትእ​ዛዝ ባሕ​ርን የገ​ሠ​ጽ​ሃት፥ ቀላ​ዮ​ችን የዘ​ጋህ፥ የሚ​ያ​ስ​ፈ​ራ​ው​ንም የወ​ሰ​ንህ፥

16 ይኸ​ውም በተ​መ​ሰ​ገ​ነው ስምህ ነው፤ ኀይ​ልህ ከመ​ገ​ለጡ የተ​ነሣ ሁሉ የሚ​ር​ድና የሚ​ን​ቀ​ጠ​ቀጥ፤

17 ለክ​ብ​ርህ ከፍ​ተ​ኛ​ነት ፍጻሜ የለ​ው​ምና፥ የቍ​ጣ​ህም መቅ​ሠ​ፍት በኃ​ጥ​አን ላይ ግሩም ነው።

18 በት​እ​ዛ​ዝህ ለሚ​ሆ​ነው ይቅ​ርታ ስፍር ቍጥር የለ​ውም፤ ገናና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አንተ ብቻ ነህና፥ ይቅር ባይ፥ ከቍጣ የራ​ቅህ፥ ይቅ​ር​ታህ የበዛ፥ የሰ​ው​ንም ኀጢ​አት የም​ታ​ስ​ተ​ሰ​ርይ አንተ ነህ።

19 አሁ​ንም አቤቱ፥ የጻ​ድ​ቃን አም​ላ​ካ​ቸው አንተ ነህ። ንስ​ሓን የፈ​ጠ​ርህ ለጻ​ድቅ ሰው አይ​ደ​ለ​ምና፥ አን​ተን ላል​በ​ደሉ ለአ​ብ​ር​ሃ​ምና ለይ​ስ​ሐቅ ለያ​ዕ​ቆ​ብም አይ​ደ​ለ​ምና፤ ነገር ግን የእ​ኔን የኃ​ጥ​ኡን ንስሓ ወደ ማየት ተመ​ለስ።

20 ቍጥሩ ከባ​ሕር አሸዋ የሚ​በ​ልጥ በደ​ልን በድ​ያ​ለ​ሁና፥ ኀጢ​አ​ቴም ብዙ ነውና፤ ከበ​ደ​ሌም ብዛት የተ​ነሣ ቀና ብዬ የሰ​ማ​ይን ርዝ​መት አይ ዘንድ አገ​ባቤ አይ​ደ​ለም። ሰው​ነ​ቴን ከኀ​ጢ​አቴ አሳ​ር​ፋት ዘንድ በብ​ረት ቀፎ ደከ​ምሁ፤ በዚ​ህም ደግሞ አላ​ረ​ፍ​ሁም፤ መዓ​ት​ህን አነ​ሣ​ሥ​ቻ​ለ​ሁና፥

21 ከን​ቱ​ውን ስመ​ለ​ከት የማ​ይ​ጠ​ቅ​መ​ኝ​ንም ነገር ሳበዛ በፊ​ትህ ክፉ ሥራን ሠር​ቻ​ለ​ሁና።

22 አሁ​ንም ቸር​ነ​ት​ህን እየ​ለ​መ​ንሁ በልቤ ጕል​በት እሰ​ግ​ዳ​ለሁ።

23 አቤቱ፥ ጌታዬ፥ ፈጽሜ በደ​ልሁ፤ ኀጢ​አ​ቴ​ንም አም​ና​ለሁ።

24 አን​ተ​ንም እማ​ል​ዳ​ለሁ፤ እለ​ም​ን​ህ​ማ​ለሁ፤ ይቅር በለኝ፤ አቤቱ፥ ይቅር በለኝ፤ ለኀ​ጢ​አ​ቴም አሳ​ል​ፈህ አት​ስ​ጠኝ።

25 ለዘ​ለ​ዓ​ለም ክፋ​ቴን አት​መ​ል​ከ​ት​ብኝ፤ በም​ድር ጥል​ቀ​ትም አት​በ​ቀ​ለኝ፤ አቤቱ፥ በን​ስሓ ለሚ​መ​ለሱ ሰዎች፥ አም​ላ​ካ​ቸው አንተ ነህና፥ ቸር​ነ​ትህ በእኔ ላይ ይገ​ለጥ፤ መዳን የማ​ይ​ገ​ባኝ ሲሆን በይ​ቅ​ር​ታህ ብዛት አዳ​ን​ኸኝ።

26 በየ​ጊ​ዜ​ውና በሕ​ይ​ወቴ ዘመን ሁሉ አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ። የሰ​ማ​ያት ኀይል ሁሉ አን​ተን ያመ​ሰ​ግ​ና​ሉና፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ምስ​ጋና ለአ​ንተ ይገ​ባል፤” አሜን። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ምናሴ ባለ​ማ​ወቅ ከአ​ደ​ረ​ገው ክፉ ሥራው እንደ ተመ​ለሰ ባየ ጊዜ ይቅር አለው፤ ጸሎ​ቱ​ንም ሰማው፤ ልመ​ና​ው​ንም ተቀ​በ​ለው፤ ወደ መን​ግ​ሥ​ቱም ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም መለ​ሰው፤ ምና​ሴም እርሱ አም​ላክ እንደ ሆነ ዐወቀ።

27 ከዚህ በኋላ በዳ​ዊት ከተማ በስ​ተ​ው​ጭው ከግ​ዮን ሰሜ​ናዊ ምዕ​ራብ በሸ​ለ​ቆው ውስጥ እስከ ዓሣ በር መግ​ቢያ ድረስ ቅጥር ሠራ። እስከ ዖፌ​ልም አዞ​ረ​በት፤ እጅ​ግም ከፍ አደ​ረ​ገው፤ በተ​መ​ሸ​ጉ​ትም በይ​ሁዳ ከተ​ሞች ሁሉ የጭ​ፍራ አለ​ቆ​ችን አኖረ።

28 እን​ግ​ዶ​ች​ንም አማ​ል​ክ​ትና ጣዖ​ታ​ቱ​ንም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አራቀ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ባለ​በት ተራራ ላይና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሠ​ራ​ቸ​ውን መሠ​ዊ​ያ​ዎች ሁሉ ወስዶ ከከ​ተ​ማ​ዪቱ በስ​ተ​ውጭ ጣላ​ቸው።

29 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም መሠ​ዊያ ደግሞ አደሰ፤ የደ​ኅ​ነ​ት​ንና የም​ስ​ጋ​ና​ንም መሥ​ዋ​ዕት ሠዋ​በት፤ የይ​ሁ​ዳም ሕዝብ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዲ​ያ​መ​ልኩ አዘዘ።

30 ሕዝቡ ግን ከአ​ም​ላ​ካ​ቸው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈጽ​መው ርቀው ገና በኮ​ረ​ብ​ታ​ዎች ላይ ይሠዉ ነበር፥

31 የም​ና​ሴም የቀ​ሩት ነገ​ሮች፥ ወደ አም​ላ​ኩም የጸ​ለ​የው ጸሎት፥ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም የነ​ገ​ሩት የነ​ቢ​ያት ቃል፥ እነሆ፥ በእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መጽ​ሐፍ ተጽ​ፈ​ዋል።

32 ደግ​ሞም ጸሎ​ቱን፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሰማው፥ ኀጢ​አ​ቱና መተ​ላ​ለፉ ሁሉ፥ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሳይ​መ​ለስ ኮረ​ብ​ታ​ውን የሠ​ራ​በት ዐፀ​ዱ​ንና የተ​ቀ​ረ​ጹ​ት​ንም ምስ​ሎች የተ​ከ​ለ​በት ስፍራ፥ እነሆ፥ በባለ ራእዩ የታ​ሪክ መጽ​ሐፍ ተጽ​ፈ​ዋል።

33 ምና​ሴም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፤ በቤ​ቱም አት​ክ​ልት ቦታ ቀበ​ሩት፤ ልጁም አሞጽ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።

34 አሞጽ መን​ገሥ በጀ​መረ ጊዜ የሃያ ሁለት ዓመት ጐል​ማሳ ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሁለት ዓመት ነገሠ።

35 አባ​ቱም ምናሴ እን​ዳ​ደ​ረገ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ አደ​ረገ፤ አሞ​ጽም አባቱ ምናሴ ለሠ​ራ​ቸው ለተ​ቀ​ረ​ጹት ምስ​ሎች ሁሉ ሠዋ፤ አመ​ለ​ካ​ቸ​ውም።

36 አባ​ቱም ምናሴ ሰው​ነ​ቱን እን​ዳ​ዋ​ረደ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ሰው​ነ​ቱን አላ​ዋ​ረ​ደም፤ ነገር ግን አሞጽ መተ​ላ​ለ​ፉን እጅግ አበዛ።

37 አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹም ተነ​ሡ​በት፤ በቤ​ቱም ገደ​ሉት።

38 የሀ​ገሩ ሕዝብ ግን በን​ጉሡ በአ​ሞጽ ላይ የተ​ነ​ሡ​ትን ሁሉ ገደሉ፤ የሀ​ገ​ሩም ሕዝብ ልጁን ኢዮ​ስ​ያ​ስን በእ​ርሱ ፋንታ አነ​ገሡ።

跟着我们:



广告