Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

2 ዜና መዋዕል 28 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የይ​ሁዳ ንጉሥ የአ​ካዝ ዘመነ መን​ግ​ሥት
( 2ነገ. 16፥1-4 )

1 አካ​ዝም መን​ገሥ በጀ​መረ ጊዜ የሃያ ዓመት ጐል​ማሳ ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ዐሥራ ስድ​ስት ዓመት ነገሠ፤ እንደ አባ​ቱም እንደ ዳዊት በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቅን ነገር አላ​ደ​ረ​ገም።

2 ነገር ግን በእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መን​ገድ ሄደ፤ ደግ​ሞም ቀል​ጠው የተ​ሠ​ሩ​ትን ምስ​ሎች ሠራ።

3 ደግ​ሞም በሄ​ኖም ልጅ ሸለቆ ውስጥ ለም​ስሉ ሠዋ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት እን​ዳ​ሳ​ደ​ዳ​ቸው እንደ አሕ​ዛ​ብም ክፉ ልማድ ልጆ​ቹን በእ​ሳት አቃ​ጠለ።

4 በኮ​ረ​ብ​ታው መስ​ገ​ጃ​ዎ​ችና በተ​ራ​ሮች ላይ በለ​መ​ለ​መ​ውም ዛፍ ሁሉ በታች ያጥን ነበር።

5 ስለ​ዚህ አም​ላኩ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሶ​ርያ ንጉሥ እጅ አሳ​ልፎ ሰጠው፤ እር​ሱም መታው፤ ከእ​ር​ሱም ብዙ ምር​ኮ​ኞ​ችን ወሰደ፤ ወደ ደማ​ስ​ቆም አመ​ጣው። ደግ​ሞም በእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ እጅ አሳ​ልፎ ሰጠው፤ እር​ሱም በታ​ላቅ አመ​ታት መታው።

6 የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትተው ነበ​ርና የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ የሮ​ሜ​ልዩ ልጅ ፋቁሔ በአ​ንድ ቀን ከይ​ሁዳ ጽኑ​ዓን የነ​በሩ መቶ ሃያ ሺህ ሰል​ፈ​ኞ​ችን ገደለ፤

7 ከኤ​ፍ​ሬም ወገን የነ​በ​ረው ኀያል ሰው ዝክ​ሪም የን​ጉ​ሡን ልጅ ማዓ​ሥ​ያ​ንና የቤ​ቱን አዛዥ ዓዝ​ሪ​ቃ​ምን፥ ለን​ጉ​ሡም በማ​ዕ​ርግ ሁለ​ተኛ የሆ​ነ​ውን ሕል​ቃ​ናን ገደለ።

8 የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሦስት መቶ ሺህ ሴቶ​ችን፥ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ች​ንም ማረኩ፤ እጅ​ግም ምርኮ ከእ​ነ​ርሱ ወስ​ደው ወደ ሰማ​ርያ አገቡ።

9 በዚ​ያም ዖዴድ የተ​ባለ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነቢይ ነበረ፤ ወደ ሰማ​ር​ያም የሚ​መ​ጣ​ውን ጭፍራ ሊገ​ና​ኘው ወጣ፤ እን​ዲ​ህም አላ​ቸው፤ “እነሆ፥ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሁ​ዳን ስለ ተቈጣ በእ​ጃ​ችሁ አሳ​ልፎ ሰጣ​ቸው፤ እና​ን​ተም ወደ ሰማይ በሚ​ደ​ርስ ቍጣ ገደ​ላ​ች​ኋ​ቸው።

10 አሁ​ንም የይ​ሁ​ዳ​ንና የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን ልጆች ባሪ​ያ​ዎች አድ​ር​ገን እን​ግዛ ትላ​ላ​ችሁ፤ የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችሁ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ክር የም​ሆን እኔም ከእ​ና​ንተ ጋር ያለሁ አይ​ደ​ለ​ምን?

11 አሁ​ንም ስሙ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ በላ​ያ​ችሁ ነድ​ዶ​አ​ልና ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ የወ​ሰ​ዳ​ች​ኋ​ቸ​ውን ምር​ኮ​ኞች መልሱ።”

12 ደግ​ሞም ከኤ​ፍ​ሬም ልጆች አለ​ቆች የአ​ናን ልጅ ዓዛ​ር​ያስ፥ የመ​ስ​ለ​ሞት ልጅ በራ​ክያ፥ የሳ​ሎም ልጅ ሕዝ​ቅ​ያስ፥ የአ​ዳሊ ልጅ አማ​ስያ ከሰ​ልፍ የተ​መ​ለ​ሱ​ትን ተቃ​ወ​ሙ​አ​ቸው።

13 “ደግ​ሞም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በእኛ ላይ በደል ታመ​ጡ​ብ​ና​ላ​ች​ሁና፥ ኀጢ​አ​ታ​ች​ን​ንና በደ​ላ​ች​ንን ታበ​ዙ​ብ​ና​ላ​ች​ሁና የተ​ማ​ረ​ኩ​ትን ወደ​ዚህ አታ​ግቡ፤ በደ​ላ​ችን ታላቅ ነውና፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የመ​ቅ​ሠ​ፍቱ ቍጣ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ነውና” አሉ​አ​ቸው።

14 ሰል​ፈ​ኞ​ቹም ምር​ኮ​ኞ​ቹ​ንና ምር​ኮ​ውን በአ​ለ​ቆ​ችና በጉ​ባኤ ሁሉ ፊት ተዉ።

15 በስ​ማ​ቸ​ውም የተ​ጻፉ ሰዎች ተነ​ሥ​ተው ምር​ኮ​ኞ​ቹን ወሰዱ፤ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም ራቁ​ታ​ቸ​ውን ለነ​በ​ሩት ሁሉ ከም​ር​ኮው አለ​በ​ሱ​አ​ቸው፤ አጐ​ና​ጸ​ፉ​አ​ቸ​ውም፤ ጫማም በእ​ግ​ራ​ቸው አደ​ረ​ጉ​ላ​ቸው፤ መገ​ቡ​አ​ቸ​ውም፤ አጠ​ጡ​አ​ቸ​ውም፤ ቀቡ​አ​ቸ​ውም፤ ደካ​ሞ​ቹ​ንም ሁሉ በአ​ህ​ዮች ላይ አስ​ቀ​መ​ጡ​አ​ቸው፤ ዘን​ባ​ባም ወዳ​ለ​በት ከተማ ወደ ኢያ​ሪኮ ወደ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው አመ​ጡ​አ​ቸው፤ ወደ ሰማ​ር​ያም ተመ​ለሱ።


ንጉሡ አካዝ የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ርዳታ እንደ ጠየቀ
( 2ነገ. 16፥7-9 )

16 በዚ​ያም ጊዜ ንጉሡ አካዝ ርዳታ ፈልጎ ወደ አሦር ንጉሥ ላከ፤

17 የኤ​ዶ​ም​ያስ ሰዎች ዳግ​መኛ መጥ​ተው፥ ይሁ​ዳ​ንም መት​ተው ብዙ ምር​ኮኛ ወስ​ደው ነበ​ርና።

18 ደግ​ሞም ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን በቆ​ላ​ውና በደ​ቡብ በኩል ባሉት በይ​ሁዳ ከተ​ሞች አደጋ ጥለው ነበር፤ ቤት​ሳ​ሚ​ስ​ንና ኤሎ​ንን፥ ጋቤ​ሮ​ት​ንም፥ ሠካ​ዕ​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን፥ ቴም​ና​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋ​ንም፥ ጋማ​ዚ​እ​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን ወስ​ደው በዚያ ተቀ​ም​ጠው ነበር።

19 በይ​ሁ​ዳም ንጉሥ በአ​ካዝ ምክ​ን​ያት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሁ​ዳን አዋ​ረ​ደው፤ እርሱ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅግ ርቆ​አ​ልና።

20 የአ​ሦ​ርም ንጉሥ ቴል​ጌ​ል​ቴ​ል​ፌ​ል​ሶር መጥቶ አስ​ጨ​ነ​ቀው።

21 አካ​ዝም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ከን​ጉ​ሡና ከአ​ለ​ቆ​ቹም ቤት የነ​በ​ረ​ውን ሁሉ ወሰደ፤ ለአ​ሦ​ርም ንጉሥ ሰጠ፥ ነገር ግን አስ​ጨ​ነ​ቀው እንጂ አል​ረ​ዳ​ውም።

22 ዳግ​መ​ኛም ንጉሡ አካዝ ፈጽሞ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ራቀ።

23 ንጉ​ሡም፥ “የመ​ቱ​ኝን የደ​ማ​ስ​ቆን አማ​ል​ክት እፈ​ል​ጋ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ የሶ​ር​ያን ንጉሥ እር​ሱን ረድ​ተ​ው​ታ​ልና እኔ​ንም ይረ​ዱኝ ዘንድ እሠ​ዋ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ” አለ። ነገር ግን ለእ​ር​ሱና ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዕን​ቅ​ፋት ሆኑ።

24 አካ​ዝም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ዕቃ​ዎች ሁሉ ወስዶ ሰባ​በ​ራ​ቸው፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤት ደጆች ዘጋ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ማዕ​ዘን ሁሉ ለራሱ መሠ​ዊያ ሠራ።

25 በይ​ሁ​ዳም ከተ​ሞች ሁሉ ለሌ​ሎች አማ​ል​ክት ያጥን ዘንድ የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎ​ችን አሠራ፤ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አስ​ቈጣ።

26 የቀ​ሩ​ትም ነገ​ሮ​ቹና ሥራው ሁሉ፥ የፊ​ተ​ኞ​ቹና የኋ​ለ​ኞቹ እነሆ፥ በይ​ሁ​ዳና በእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መጽ​ሐፍ ተጽ​ፈ​ዋል።

27 አካ​ዝም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ ቀበ​ሩት፤ ነገር ግን ወደ እስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መቃ​ብር አላ​ገ​ቡ​ትም፤ ልጁም ሕዝ​ቅ​ያስ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።

跟着我们:



广告