Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

1 ዜና መዋዕል 26 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በረ​ኞች

1 በረ​ኞ​ችም እን​ደ​ዚህ ተመ​ደቡ፤ ከቆ​ሬ​ያ​ው​ያን ከአ​ሳፍ ልጆች የቆሬ ልጅ ሜሱ​ላም።

2 ሜሱ​ላ​ምም ልጆች ነበ​ሩት፤ በኵሩ ዘካ​ር​ያስ፥ ሁለ​ተ​ኛው ይዲ​ኤል፥ ሦስ​ተ​ኛው ዘባ​ድያ፥ አራ​ተ​ኛው የት​ን​ኤል፤

3 አም​ስ​ተ​ኛው ኤላም፥ ስድ​ስ​ተ​ኛው ይሆ​ሐ​ናን፥ ሰባ​ተ​ኛው ኤሊ​ሆ​ዔ​ናይ።

4 ዖቤ​ድ​ኤ​ዶ​ምም ልጆች ነበ​ሩት፤ በኵሩ ሰማያ፥ ሁለ​ተ​ኛው ዮዛ​ባት፥ ሦስ​ተ​ኛው ኢዮ​አስ፥ አራ​ተ​ኛው ሣካር፥ አም​ስ​ተ​ኛው ናት​ና​ኤል፤

5 ስድ​ስ​ተ​ኛው ዓሚ​ኤል፥ ሰባ​ተ​ኛው ይሳ​ኮር፥ ስም​ን​ተ​ኛው ፒላቲ ነበሩ፤ አም​ላኩ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባር​ኮ​ታ​ልና።

6 ለልጁ ለሰ​ማ​ያም ከበ​ኵር ልጁ ከሮሲ ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ለት፤ እነ​ር​ሱም በአ​ባ​ታ​ቸው ቤት የሠ​ለ​ጠኑ እጅ​ግም ኀያ​ላን ነበሩ።

7 የሰ​ማያ ልጆች ዖትኒ፥ ራፋ​ኤል፥ ዖቤድ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም ኀያ​ላን የነ​በሩ ኤል​ዛ​ባድ፥ ኤሊሁ፥ ሰማ​ክያ፥ ኢስ​ባ​ኮም።

8 እነ​ዚህ ሁሉ የዖ​ቤ​ድ​ኤ​ዶም ልጆች ነበሩ፤ እነ​ር​ሱም፥ ልጆ​ቻ​ቸ​ውም፥ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ለማ​ገ​ል​ገል ኀያ​ላን የነ​በሩ የዖ​ቤ​ድ​ኤ​ዶም ልጆች ስድሳ ሁለት ነበሩ።

9 ለሜ​ሱ​ላ​ምም ኀያ​ላን የነ​በሩ ዐሥራ ስም​ንት ልጆ​ችና ወን​ድ​ሞች ነበ​ሩት።

10 ከሜ​ራ​ሪም ልጆች ለነ​በ​ረው ለሖሳ ፊተ​ኛ​ውን በር የሚ​ጠ​ብቁ ልጆች ነበ​ሩት፤ አለ​ቃ​ውም ሰምሪ ነበረ፤ በኵር አል​ነ​በ​ረም፤ አባቱ ግን አለቃ አደ​ረ​ገው፤

11 ሁለ​ተ​ኛ​ውም ኬል​ቅ​ያስ፥ ሦስ​ተ​ኛ​ውም ጥበ​ልያ፥ አራ​ተ​ኛ​ውም ዘካ​ር​ያስ ነበረ፤ የሖሳ ልጆ​ችና ወን​ድ​ሞች ሁሉ ዐሥራ ሦስት ነበሩ።

12 እንደ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሆነው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ የበ​ረ​ኞች አለ​ቆች በየ​ሰ​ሞ​ና​ቸው የሚ​ጠ​ብቁ እነ​ዚህ ነበሩ።

13 በበ​ሩም ሁሉ ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ቤቶች ታና​ሹና ታላቁ ተካ​ክ​ለው ዕጣ ተጣ​ጣሉ።

14 የም​ሥ​ራ​ቁም በር ዕጣ ለሰ​ሌ​ም​ያና ለዘ​ካ​ርያ ወደቀ። የዮ​አ​ስም ልጆች ለም​ል​ክያ ዕጣ ጣሉ፤ ዕጣ​ውም በሰ​ሜን በኩል ወጣ።

15 ለአ​ብ​ዲ​ዶም በደ​ቡብ በኩል በዕቃ ቤት አን​ጻር ዕጣ ወጣ።

16 ለሶ​ፊ​ምና ለሖ​ሳም በም​ዕ​ራብ በኩል በዐ​ቀ​በቱ መን​ገድ ባለው በሸ​ለ​ኬት በር በኩል ጥበቃ በጥ​በቃ ላይ ዕጣ ወጣ።

17 በም​ሥ​ራቅ በኩል ለየ​ዕ​ለቱ ስድ​ስት፥ በሰ​ሜን በኩል ለየ​ዕ​ለቱ አራት፥ በደ​ቡብ በኩል ለየ​ዕ​ለቱ አራት፥ ለዕቃ ቤትም ሁለት ሁለት ነበሩ።

18 በኦ​ሳም በም​ዕ​ራብ በኩል በሸ​ለ​ኬት በር ሦስት፥ በም​ሥ​ራቅ በኩል በዐ​ቀ​በቱ በር ከጥ​በቃ በላይ ጥበቃ በቀን ስድ​ስት፥ በሰ​ሜን በኩል አራት፥ በደ​ቡብ በኩል አራት፥ በዕቃ ቤቱ በኩል ተቀ​ባ​ባ​ዮች ሁለት ሁለት፥ በም​ዕ​ራብ በኩል አራት በመ​ተ​ላ​ለ​ፊ​ያ​ውም መን​ገድ ተቀ​ባ​ባ​ዮች ሁለት ሁለት።

19 ከቆ​ሬና ከሜ​ራሪ ልጆች የነ​በሩ የበ​ረ​ኞች ሰሞን ይህች ናት።

20 ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሌዋ​ው​ያ​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በሚ​ሆኑ ቤተ መዛ​ግ​ብ​ትና በን​ዋየ ቅድ​ሳቱ ቤተ መዛ​ግ​ብት ላይ ተሹ​መው ነበር።

21 የለ​አ​ዳን ልጆች፤ ለለ​አ​ዳን የሆኑ የጌ​ድ​ሶ​ና​ው​ያን ልጆች፥ ለጌ​ድ​ሶ​ና​ዊው ለለ​አ​ዳን የሆኑ፥ የአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች ይሔ​ኤሊ፤

22 የይ​ሔ​ኤሊ ልጆች፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት በሚ​ሆኑ ቤተ መዛ​ግ​ብት ላይ የነ​በሩ ዜቶም፥ ወን​ድ​ሙም ኢዮ​ኤል ነበረ።

23 ከእ​ን​በ​ረ​ማ​ው​ያን፥ ከይ​ስ​ዓ​ራ​ው​ያን፥ ከኬ​ብ​ሮ​ና​ው​ያን፥ ከዑ​ዝ​ኤ​ላ​ው​ያን፤

24 የሙሴ ልጅ የጌ​ር​ሳም ልጅ ሱባ​ኤል በቤተ መዛ​ግ​ብት ላይ ተሾሞ ነበር።

25 ወን​ድ​ሞ​ቹም፤ ከአ​ል​ዓ​ዛር ልጁ ረዓ​ብያ፥ ልጁም የሳያ፥ ልጁም ኢዮ​ራም፥ ልጁም ዝክሪ፥ ልጁም ሰሎ​ሚት ነበሩ።

26 ይህ ሰሎ​ሚ​ትና ወን​ድ​ሞቹ፥ ንጉሡ ዳዊ​ትና የአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች፥ ሻለ​ቆ​ችና የመቶ አለ​ቆች፥ የሠ​ራ​ዊ​ቱም አለ​ቆች፥ በቀ​ደ​ሱት በን​ዋየ ቅድ​ሳቱ ቤተ መዛ​ግ​ብት ሁሉ ላይ ተሹ​መው ነበር።

27 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ ሕንጻ ወደ ኋላ እን​ዳ​ይል ዳዊት ከየ​ሀ​ገሩ በማ​ረ​ካ​ቸ​ውና በሰ​በ​ሰ​ባ​ቸው በቀ​ደ​ሳ​ቸ​ውም ላይ የተ​ሾሙ ናቸው።

28 ነቢዩ ሳሙ​ኤል፥ የቂ​ስም ልጅ ሳኦል፥ የኔ​ርም ልጅ አበ​ኔር፥ የሶ​ር​ህ​ያም ልጅ ኢዮ​አብ የቀ​ደ​ሱት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ንዋየ ቅድ​ሳት ሁሉ ከሰ​ሎ​ሚ​ትና ከወ​ን​ድ​ሞቹ እጅ በታች ነበረ።

29 ከይ​ሰ​ዓ​ራ​ው​ያን ከና​ን​ያና ልጆቹ ጻፎ​ችና ፈራ​ጆች ይሆኑ ዘንድ በው​ጭው ሥራ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ተሾ​መው ነበር።

30 ከኬ​ብ​ሮ​ና​ው​ያን ሐሳ​ብ​ያና ወን​ድ​ሞቹ፥ ጽኑ​ዓን የነ​በ​ሩት ሺህ ሰባት መቶ ሰዎች፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራ ሁሉ፥ ለን​ጉ​ሡም አገ​ል​ግ​ሎት በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ በም​ዕ​ራብ በኩል ባለው በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ተሾ​መው ነበር።

31 ከኬ​ብ​ሮ​ና​ው​ያ​ንም እንደ አባ​ቶች ቤቶች ትው​ል​ዶች የኬ​ብ​ሮ​ና​ው​ያን አለቃ ኤር​ያስ ነበረ። ዳዊት በነ​ገሠ በአ​ር​ባ​ኛው ዓመት ይፈ​ል​ጉ​አ​ቸው ነበረ፤ በእ​ነ​ር​ሱም መካ​ከል በገ​ለ​ዓድ ኢያ​ዜር ጽኑ​ዓን ኀያ​ላን ሰዎች ተገኙ፤

32 ወን​ድ​ሞ​ቹም ጽኑ​ዓን የነ​በ​ሩት የአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ነበሩ። ንጉ​ሡም ዳዊት በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ሁሉና በን​ጉሡ ትእ​ዛዝ ሁሉ በሮ​ቤ​ላ​ው​ያ​ንና በጋ​ዳ​ው​ያን፥ በም​ና​ሴም ነገድ እኩ​ሌታ ላይ ሹሞች አደ​ረ​ጋ​ቸው።

跟着我们:



广告