Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

1 ዜና መዋዕል 15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ለማ​ም​ጣት የተ​ደ​ረገ ዝግ​ጅት

1 ዳዊ​ትም በከ​ተ​ማው ለራሱ ቤቶ​ችን ሠራ፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ታቦት ስፍራ አዘ​ጋጀ፤ ድን​ኳ​ንም ተከ​ለ​ላት።

2 በዚ​ያን ጊዜም ዳዊት፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ይሸ​ከሙ ዘንድ፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ያገ​ለ​ግ​ሉት ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከመ​ረ​ጣ​ቸው ከሌ​ዋ​ው​ያን በቀር ማንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ይሸ​ከም ዘንድ አይ​ገ​ባ​ውም” አለ።

3 ዳዊ​ትም ወዳ​ዘ​ጋ​ጀ​ላት ስፍራ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ያመጣ ዘንድ እስ​ራ​ኤ​ልን ሁሉ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሰበ​ሰበ።

4 ዳዊ​ትም የአ​ሮ​ንን ልጆ​ችና ሌዋ​ው​ያ​ንን ሰበ​ሰበ።

5 ከቀ​ዓት ልጆች፤ አለ​ቃው ኡር​ኤል፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም መቶ ሃያ፤

6 ከሜ​ራሪ ልጆ​ችም፤ አለ​ቃው ዓሣያ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም ሁለት መቶ ኀምሳ፤

7 ከጌ​ድ​ሶን ልጆች፤ አለ​ቃው ኢዮ​ሔት፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም መቶ ሠላሳ፤

8 ከኤ​ል​ሳ​ፋን ልጆች፤ አለ​ቃው ሰማያ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም ሁለት መቶ፤

9 ከኬ​ብ​ሮን ልጆች፤ አለ​ቃው ኢዮ​ሔል፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም ሰማ​ንያ፤

10 ከዑ​ዝ​ኤል ልጆች፤ አለ​ቃው አሚ​ና​ዳብ፥ ወን​ድ​ሞ​ቹም መቶ ዐሥራ ሁለት።

11 ዳዊ​ትም ካህ​ና​ቱን ሳዶ​ቅ​ንና አብ​ያ​ታ​ርን፥ ሌዋ​ው​ያ​ን​ንም፥ ኡር​ኤ​ልን፥ ዓሣ​ያን፥ ኢዮ​ኤ​ልን፥ ሰማ​ያን፥ ኤሊ​ኤ​ልን፥ አሚ​ና​ዳ​ብ​ንም ጠርቶ፦

12 “እና​ንተ የሌ​ዋ​ው​ያን አባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች ናችሁ፤ ወዳ​ዘ​ጋ​ጀ​ሁ​ላት ስፍራ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ታመጡ ዘንድ እና​ን​ተና ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ ተቀ​ደሱ።

13 በቀ​ድሞ ሥራ​ችን አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እርስ በር​ሳ​ችን አላ​ጠ​ፋ​ንም፤ በጦ​ር አል​ፈ​ለ​ገ​ን​ምና” አላ​ቸው።

14 የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት ያመጡ ዘንድ ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ ራሳ​ቸ​ውን አነጹ።

15 በመ​ጽ​ሐ​ፍም እንደ ተጻፈ ሙሴ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል እንደ አዘ​ዛ​ቸው የሌ​ዋ​ው​ያን ልጆች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት በት​ከ​ሻ​ቸው ላይ በመ​ሎ​ጊ​ያ​ዎቹ ተሸ​ከሙ። መባ​እና ቍር​ባ​ንም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ነበረ።

16 ዳዊ​ትም በዜማ ዕቃ፥ በመ​ሰ​ን​ቆና በበ​ገና፥ በጸ​ና​ጽ​ልም እን​ዲ​ያ​ዜሙ፥ ድም​ፃ​ቸ​ው​ንም በደ​ስታ ከፍ እን​ዲ​ያ​ደ​ርጉ መዘ​ም​ራ​ኑን “ወን​ድ​ሞ​ቻ​ች​ሁን ሹሙ” ብሎ ለሌ​ዋ​ው​ያን አለ​ቆች ተና​ገረ።

17 ሌዋ​ው​ያ​ኑም የኢ​ዩ​ኤ​ልን ልጅ ኤማ​ንን፥ ከወ​ን​ድ​ሞ​ቹም የበ​ራ​ክ​ያን ልጅ አሳ​ፍን፥ ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ከሜ​ራሪ ልጆች የቂ​ሳ​ንን ልጅ ኢታ​ንን፥

18 ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር በሁ​ለ​ተ​ኛው ተራ የሆ​ኑ​ትን ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውን ዘካ​ር​ያ​ስን፥ ቤንን፥ አዝ​ኤ​ልን፥ ስሜ​ራ​ሞ​ትን፥ ኢያ​ሄ​ልን፥ ኡኒን፥ ኤል​ያ​ብን፥ በና​እ​ያን፥ መዕ​ሤ​ያን፥ መታ​ት​ያን፥ ኤል​ፋ​ይን፥ ሜቄ​ድ​ያን፥ በረ​ኞ​ች​ንም አብ​ዲ​ዶ​ምን፥ ኢያ​ኤ​ል​ንና ዖዝ​ያ​ስን አቆሙ።

19 መዘ​ም​ራ​ንም ኤማ​ንና አሳፍ ኤታ​ንም በናስ ጸና​ጽል ከፍ አድ​ር​ገው ያሰሙ ነበር።

20 ዘካ​ር​ያስ፥ አዝ​ኤል፥ ሰሚ​ራ​ሞት፥ ኢያ​ሔል፥ ዑኒ፥ ኤል​ያብ፥ መዕ​ሤያ፥ በና​ያስ በመ​ሰ​ንቆ በል​ዑል ቃል ያዜሙ ነበር።

21 ማታ​ት​ያስ፥ ኤል​ፋ​ላይ፥ ሜቄ​ድ​ያስ፥ አብ​ዴ​ዶም፥ ይዒ​ኤል፥ ዖዝ​ያ​ስም ስም​ንት አው​ታር ባለው በገና ይዘ​ምሩ ነበር።

22 የሌ​ዋ​ው​ያ​ኑም አለቃ ኮነ​ን​ያስ በዜማ ላይ ተሾሞ ነበር። ብል​ሃ​ተኛ ነበ​ረና።

23 በራ​ክ​ያና ሕል​ቃ​ናም ለታ​ቦቷ በረ​ኞች ነበሩ።

24 ካህ​ና​ቱም ሰበ​ንያ፥ ኢዮ​ሣ​ፍጥ፥ ናት​ና​ኤል፥ ዓማ​ሣይ፥ ዘካ​ር​ያስ፥ በና​ያስ፥ አል​ዓ​ዛ​ርም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታቦት ፊት መለ​ከት ይነፉ ነበር። አብ​ዲ​ዶ​ምና ኢያ​ኤ​ያም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታቦት በረ​ኞች ነበሩ።

25 ዳዊ​ትም፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሽማ​ግ​ሌ​ዎች፥ የሻ​ለ​ቆ​ችም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የቃል ኪዳ​ኑን ታቦት ከአ​ቢ​ዳራ ቤት በደ​ስታ ያመጡ ዘንድ ሄዱ።

26 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቃል ኪዳን ታቦት የተ​ሸ​ከ​ሙ​ትን ሌዋ​ው​ያ​ንን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በአ​በ​ረ​ታ​ቸው ጊዜ ሰባት በሬ​ዎ​ች​ንና ሰባት አውራ በጎ​ችን ሠዉ።

27 ዳዊ​ትም፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የቃል ኪዳ​ኑን ታቦት የተ​ሸ​ከሙ ሌዋ​ው​ያ​ንም ሁሉ፥ መዘ​ም​ራ​ኑም፥ የመ​ዘ​ም​ራ​ኑም አለቃ ኮኖ​ን​ያስ የጥሩ በፍታ ቀሚስ ለብ​ሰው ነበር፤ ዳዊ​ትም የከ​በረ ልብስ ለብሶ ነበረ።

28 እን​ዲሁ እስ​ራ​ኤል ሁሉ በይ​ባቤ፥ ቀንደ መለ​ከ​ትና እን​ቢ​ልታ እየ​ነፉ፥ ጸና​ጽ​ልና መሰ​ን​ቆም፥ በገ​ናም እየ​መቱ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የቃል ኪዳን ታቦት አመጡ።

29 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ኪዳን ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ በደ​ረ​ሰች ጊዜ የሳ​ኦል ልጅ ሜል​ኮል በመ​ስ​ኮት ሆና ተመ​ለ​ከ​ተች፤ ንጉ​ሡም ዳዊት ሲዘ​ፍ​ንና ሲጫ​ወት አይታ በል​ብዋ ናቀ​ችው።

跟着我们:



广告