መዝሙር 124 - አዲሱ መደበኛ ትርጒምመዝሙር 124 የዳዊት መዝሙረ መዓርግ። 1 እስራኤል እንዲህ ይበል፤ እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣ 2 ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣ 3 ቍጣቸው በላያችን በነደደ ጊዜ፣ በቁመናችን በዋጡን ነበር፤ 4 ጐርፍ ባጥለቀለቀን፣ ፈረሰኛው ውሃ ባሰጠመን፣ 5 ደራሽ ውሃም ጠራርጎ በወሰደን ነበር። 6 በጥርሳቸው ከመዘንጠል የጠበቀን፣ እግዚአብሔር ይባረክ። 7 ነፍሳችን እንደ ወፍ፣ ከዐዳኝ ወጥመድ አመለጠች፤ ወጥመዱ ተሰበረ፤ እኛም አመለጥን። 8 የሰማይና የምድር ፈጣሪ፣ የእግዚአብሔር ስም ረዳታችን ነው። |
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
Biblica, Inc.