ነህምያ 7 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም1 ቅጥሩ እንደ ገና ከተሠራና መዝጊያዎቹንም በየቦታቸው ከገጠምሁ በኋላ፣ በር ጠባቂዎች፣ መዘምራንና ሌዋውያን ተመደቡ። 2 በኢየሩሳሌምም ላይ ወንድሜን አናኒን እንዲሁም ፍጹም ታማኝና ከሌሎች ሰዎች ይልቅ እግዚአብሔርን ይበልጥ የሚፈራውን የግንቡን አዛዥ ሐናንያን ኀላፊ አደረግኋቸው። 3 ለእነርሱም፣ “የኢየሩሳሌም በሮች ፀሓይ ሞቅ እስክትል ድረስ አይከፈቱም፤ በር ጠባቂዎቹ ዘብ በሚቆሙበት ጊዜ ሁሉ፣ በሮቹን ይዝጓቸው፤ መወርወሪያም ያድርጉባቸው፣ እንዲሁም ከኢየሩሳሌም ነዋሪዎች አንዳንዶቹን በየጥበቃ ቦታቸው፣ አንዳንዶቹን ደግሞ በየቤታቸው አጠገብ እንዲቆሙ መድቡ” አልኋቸው። ከምርኮ የተመለሱት ሰዎች ዝርዝር 4 ከተማዪቱ ታላቅና ሰፊ ነበረች፤ የሚኖርባት ሕዝብ ግን ጥቂት ሲሆን፣ ቤቶች ገና አልተሠሩባትም ነበር። 5 ስለዚህ መኳንንቱን፣ ሹማምቱንና ተራውን ሕዝብ ሰብስቤ በየቤተ ሰቡ ይመዘገቡ ዘንድ እግዚአብሔር ይህን በልቤ አኖረ። ወደ ምድራቸው ለመመለስ የመጀመሪያ የሆኑትን ሰዎች የትውልድ ሐረግ መዝገብ አገኘሁ፤ ተጽፎ ያገኘሁትም ይህ ነው። 6 የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ማርኮ ከወሰዳቸው ምርኮኞች መካከል የተመለሱት የአውራጃው ተወላጆች እነዚህ ናቸው፤ እያንዳንዳቸውም በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ወደሚገኙት ወደ የራሳቸው ከተሞች ተመለሱ። 7 የመጡትም ከዘሩባቤል፣ ከኢያሱ፣ ከነህምያ፣ ከዓዛርያስ፣ ከረዓምያ፣ ከነሐማኒ፣ ከመርዶክዮስ፣ ከበላሳን፣ ከሚስጴሬት፣ ከበጉዋይ፣ ከነሑምና ከበዓና ጋራ ነው። የእስራኤል ሰዎች ዝርዝር፦ 8 የፋሮስ ዘሮች 2,172 9 የሰፋጥያስ ዘሮች 372 10 የኤራ ዘሮች 652 11 የኢያሱና የኢዮአብ ዘር የሆኑት የፈሐት ሞዓብ ዘሮች 2,818 12 የኤላም ዘሮች 1,254 13 የዛቱዕ ዘሮች 845 14 የዘካይ ዘሮች 760 15 የቢንዊ ዘሮች 648 16 የቤባይ ዘሮች 628 17 የዓዝጋድ ዘሮች 2,322 18 የአዶኒቃም ዘሮች 667 19 የበጉዋይ ዘሮች 2,067 20 የዓዲን ዘሮች 655 21 በሕዝቅያስ የትውልድ ሐረግ የአጤር ዘሮች 98 22 የሐሱም ዘሮች 328 23 የቤሳይ ዘሮች 324 24 የሐሪፍ ዘሮች 112 25 የገባዖን ዘሮች 95 26 የቤተ ልሔምና የነጦፋ ሰዎች 188 27 የዓናቶት ሰዎች 128 28 የቤት አዝሞት ሰዎች 42 29 የቂርያትይዓይሪም፣ የከፊራና የብኤሮት ሰዎች 743 30 የራማና የጌባዕ ሰዎች 621 31 የማክማስ ሰዎች 122 32 የቤቴልና የጋይ ሰዎች 123 33 የሌላው ናባው ሰዎች 52 34 የሌላው ኤላም ዘሮች 1,254 35 የካሪም ዘሮች 320 36 የኢያሪኮ ዘሮች 345 37 የሎድ፣ የሐዲድና የኦኖም ዘሮች 721 38 የሴናዓ ዘሮች 3,930 39 ካህናቱ፦ ከኢያሱ ቤተ ሰብ የዮዳኤ ዘሮች 973 40 የኢሜር ዘሮች 1,052 41 የፋስኮር ዘሮች 1,247 42 የካሪም ዘሮች 1,017 43 ሌዋውያኑ፦ በሆዳይዋ በኩል የኢያሱና የቀድምኤል ዘሮች 74 44 መዘምራኑ፦ የአሳፍ ዘሮች 148 45 በር ጠባቂዎቹ፦ የሰሎም፣ የአጤር፣ የጤልሞን፣ የዓቁብ፣ የሐጢጣና የሶባይ ዘሮች 138 46 የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች፦ የሲሐ፣ የሐሡፋ፣ የጠብዖት ዘሮች፣ 47 የኬራስ፣ የሲዓ፣ የፋዶን፣ 48 የልባና፣ የአጋባ፣ የሰምላይ ዘሮች፣ 49 የሐናን፣ የጌዴል፣ የጋሐር ዘሮች፣ 50 የራያ፣ የረአሶን፣ የኔቆዳ ዘሮች፣ 51 የጋሴም፣ የዖዛ፣ የፋሴሐ ዘሮች፣ 52 የቤሳይ፣ የምዑኒም፣ የንፉሰሲም ዘሮች፣ 53 የበቅቡቅ፣ የሐቁፋ፣ የሐርሑር ዘሮች፣ 54 የበስሎት፣ የምሒዳ፣ የሐርሳ ዘሮች፣ 55 የበርቆስ፣ የሲሣራ፣ የቴማ ዘሮች፣ 56 የንስያና፣ የሐጢፋ ዘሮች። 57 የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች፦ የሶጣይ፣ የሶፌሬት፣ የፍሩዳ ዘሮች፣ 58 የየዕላ፣ የደርቆን፣ የጌዴል ዘሮች፣ 59 የሰፋጥያስ፣ የሐጢል፣ የፈክራት ሐፂቦይምና የአሞን ዘሮች። 60 የቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች 392 61 ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ደግሞ ከቴልሜላ፣ ከቴላሬሳ፣ ከክሩብ፣ ከአዳንና ከኢሜር የመጡ ናቸው፤ ይሁን እንጂ ዘሮቻቸው ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ማስረዳት አልቻሉም፦ 62 የዳላያ፣ የጦብያና፣ የኔቆዳ ዘሮች 642 63 ከካህናቱ መካከል፦ የኤብያ፣ የአቆስ፣ የቤርዜሊ ዘሮች፤ ይህ ሰው የገለዓዳዊውን የቤርዜሊን ሴት ልጅ አግብቶ በዚሁ ስም ለመጠራት በቅቷል። 64 እነዚህ በትውልድ መዝገቡ ውስጥ የቤተ ሰባቸውን ዝርዝር ፈለጉ፤ ነገር ግን ሊያገኙት አልቻሉም፤ ስለዚህ እንዳልነጹ ተቈጥረው ከክህነት ተከለከሉ። 65 ስለዚህ አገረ ገዥውም ኡሪምና ቱሚም የሚይዝ ካህን እስኪነሣ ድረስ እጅግ ከተቀደሰው ምግብ እንዳይበሉ አዘዛቸው። 66 የማኅበሩ ቍጥር በሙሉ 42,360 ነበር፤ 67 ይህም 7,337 ከሚሆኑት ከወንዶችና ከሴቶች አገልጋዮቻቸው በተጨማሪ ነው፤ 245 ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሯቸው። 68 736 ፈረሶች፣ 245 በቅሎዎች፣ 435 ግመሎችና 69 6,720 አህዮችም ነበሯቸው። 70 አንዳንድ የየቤተ ሰቡ አባቶች ለሥራው መዋጮ አደረጉ፤ አገረ ገዥውም 1,000 የወርቅ ዳሪክ፣ 50 ድስቶች፣ 530 አልባሰ ተክህኖ ለግምጃ ቤቱ ሰጠ። 71 ከየቤተ ሰቡ አባቶችም አንዳንዶች ለሥራው የሚሆን 20,000 የወርቅ ዳሪክ 2,200 ምናን ብር ለግምጃ ቤቱ ሰጡ። 72 የቀረው ሕዝብ በአጠቃላይ የሰጠው 20,000 የወርቅ ዳሪክ 2,000 ምናን ብርና 67 ልብሰ ተክህኖ ነበር። 73 ካህናቱ፣ ሌዋውያኑ፣ በር ጠባቂዎቹ፣ መዘምራኑና የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች፣ ከሕዝቡም የተወሰነው ክፍልና የቀሩት እስራኤላውያን በየራሳቸው ከተሞች ሰፈሩ። ሰባተኛው ወር በደረሰና እስራኤላውያን ሁሉ በየከተሞቻቸው በተቀመጡ ጊዜ፣ |
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
Biblica, Inc.