Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ዕዝራ 2 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም


ወደ አገራቸው የተመለሱ ምርኮኞች ዝርዝር
2፥1-70 ተጓ ምብ – ነህ 7፥6-73

1 የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ማርኮ ከወሰዳቸው መካከል ከምርኮ ተመልሰው ወደ የራሳቸው ከተሞች፣ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ የመጡት የአገሩ ልጆች እነዚህ ናቸው፤

2 የመጡትም ከዘሩባቤል፣ ከኢያሱ፣ ከነህምያ፣ ከሠራያ፣ ከረዕላያ፣ ከመርዶክዮስ፣ ከበላሳን፣ ከመሴፋር፣ ከበጉዋይ፣ ከሬሁም፣ ከበዓና ጋራ ነበር። የተመለሱት የእስራኤል ሰዎች ዝርዝር የሚከተለው ነው፦

3 የፋሮስ ዘሮች 2,172

4 የሰፋጥያስ ዘሮች 372

5 የኤራ ዘሮች 775

6 የኢያሱና የኢዮአብ ዘር የሆኑት የፈሐት ሞዓብ ዘሮች 2,812

7 የኤላም ዘሮች 1,254

8 የዛቱዕ ዘሮች 945

9 የዘካይ ዘሮች 760

10 የባኒ ዘሮች 642

11 የቤባይ ዘሮች 623

12 የዓዝጋድ ዘሮች 1,222

13 የአዶኒቃም ዘሮች 666

14 የበጉዋይ ዘሮች 2,056

15 የዓዲን ዘሮች 454

16 በሕዝቅያስ የትውልድ ሐረግ የአጤር ዘሮች 98

17 የቤሳይ ዘሮች 323

18 የዮራ ዘሮች 112

19 የሐሱም ዘሮች 223

20 የጋቤር ዘሮች 95

21 የቤተ ልሔም ሰዎች 123

22 የነጦፋ ሰዎች 56

23 የዓናቶት ሰዎች 128

24 የዓዝሞት ዘሮች 42

25 የቂርያትይዓይሪም፣ የከፊራና የብኤሮት ሰዎች 743

26 የራማና የጌባዕ ዘሮች 621

27 የማክማስ ሰዎች 122

28 የቤቴልና የጋይ ሰዎች 223

29 የናባው ዘሮች 52

30 የመጌብስ ዘሮች 156

31 የሌላው ኤላም ዘሮች 1,254

32 የካሪም ዘሮች 320

33 የሎድ፣ የሐዲድና የኦኖ 725

34 የኢያሪኮ ሰዎች 345

35 የሴናዓ ዘሮች 3,630

36 ካህናቱ፦ ከኢያሱ ቤተ ሰብ የዮዳኤ ዘሮች 973

37 የኢሜር ዘሮች 1,052

38 የፋስኮር ዘሮች 1,247

39 የካሪም ዘሮች 1,017

40 ሌዋውያኑ፦ በሆዳይዋ በኩል የኢያሱና የቀድምኤል ዘሮች 74

41 መዘምራኑ፦ የአሳፍ ዘሮች 128

42 የቤተ መቅደስ በር ጠባቂዎቹ፦ የሰሎም፣ የአጤር፣ የጤልሞን፣ የዓቁብ፣ የሐጢጣና የሶባይ ዘሮች 139

43 የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች፦ የሲሐ፣ የሐሡፋ የጠብዖት ዘሮች፤

44 የኬራስ፣ የሲዓ፣ የፋዶን ዘሮች፤

45 የልባና፣ የአጋባ፣ የዓቁብ ዘሮች፤

46 የአጋብ፣ የሰምላይ፣ የሐናን ዘሮች፤

47 የጌዴል፣ የጋሐር፣ የራያ፤

48 የረአሶን፣ የኔቆዳ፣ የጋሴም ዘሮች፤

49 የዖዛ፣ የፋሴሐ፣ የቤሳይ፤

50 የአስና፣ የምዑኒም፣ የንፉሰሲም ዘሮች፤

51 የበቅቡቅ፣ የሐቁፋ፣ የሐርሑር ዘሮች፤

52 የበስሎት፣ የምሒዳ፣ የሐርሳ ዘሮች፤

53 የበርቆስ፣ የሲሣራ፣ የቴማ ዘሮች፤

54 የንስያና የሐጢፋ ዘሮች፤

55 የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች፦ የሶጣይ፣ የሶፌሬት፣ የፍሩዳ ዘሮች፤

56 የየዕላ፣ የደርቆን፣ የጌዴል ዘሮች፤

57 የሰፋጥያስ፣ የሐጢል፣ የፈክራት ሐፂቦይምና፣ የአሚ ዘሮች፤

58 የቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች 392

59 ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ደግሞ ከቴልሜላ፣ ከቴላሬሳ፣ ከክሩብ፣ ከአዳንና ከኢሜር የመጡ ናቸው፤ ይሁን እንጂ ዘሮቻቸው ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ማስረዳት አልቻሉም፦

60 የዳላያ፣ የጦብያና የኔቆዳ ዘሮች 652

61 ከካህናቱ መካከል፦ የኤብያ፣ የአቆስ፣ የቤርዜሊ ዘሮች፤ ይህ ሰው የገለዓዳዊውን የቤርዜሊን ሴት ልጅ አግብቶ በዚሁ ስም ለመጠራት በቅቷል።

62 እነዚህ በትውልድ መዝገቡ ውስጥ የቤተ ሰባቸውን ዝርዝር ፈለጉ፤ ነገር ግን ሊያገኙት አልቻሉም፤ ስለዚህ እንዳልነጹ ተቈጥረው ከክህነት ተከለከሉ።

63 አገረ ገዥውም ኡሪምና ቱሚም የሚይዝ ካህን እስኪነሣ ድረስ እጅግ ከተቀደሰው ምግብ እንዳይበሉ አዘዛቸው።

64 የማኅበሩ ቍጥር በሙሉ 42,360 ነበር፤

65 ይህም 7,337 ከሚሆኑት ከወንዶችና ከሴቶች አገልጋዮቻቸው በተጨማሪ ነው፤ 200 ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሯቸው።

66 736 ፈረሶች፣ 245 በቅሎዎች፣

67 435 ግመሎችና 6,720 አህዮች ነበሯቸው።

68 በኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ እግዚአብሔር ቤት በደረሱ ጊዜ፣ አንዳንድ የቤተ ሰብ መሪዎች በቀድሞው ቦታ እንደ ገና ለሚሠራው የእግዚአብሔር ቤት በበጎ ፈቃድ ስጦታ አደረጉ።

69 እንደየችሎታቸውም 61,000 የወርቅ ዳሪክ፣ 5,000 ምናን ብር፣ 100 ልብሰ ተክህኖ ለግምጃ ቤቱ ሰጡ።

70 ካህናቱ፣ ሌዋውያኑ፣ መዘምራኑ፣ በር ጠባቂዎቹና የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች፣ ከሌሎች ሰዎች ጋራ በየራሳቸው ከተሞች ሰፈሩ፤ የቀሩት እስራኤላውያንም በየራሳቸው ከተሞች ሰፈሩ።

መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™

የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.

በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።

The Holy Bible, New Amharic Standard Version™

Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.

Used with permission. All rights reserved worldwide. 

Biblica, Inc.
跟着我们:



广告