Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ኢዮብ 25 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም


ቢልዳድ

1 ሹሐዊው ቢልዳድ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2 “ሥልጣንና መፈራት የእግዚአብሔር ነው፤ በላይኛው ግዛቱ በሰማይ ሰላምን ይመሠርታል።

3 የሠራዊቱ ብዛት ሊቈጠር ይቻላልን? የእርሱ ብርሃንስ የማያበራለት ማነው?

4 እንዴት ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ሆኖ ሊገኝ ይችላል? ሰብአዊ ፍጡር ሆኖ እንዴት ንጹሕ ሊሆን ይችላል?

5 እነሆ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጨረቃ እንኳ ደማቅ አይደለችም፤ ከዋክብትም በእርሱ ፊት ንጹሖች አይደሉም።

6 በስባሽና ትል የሆነው ሟች ሰውማ ምንኛ የባሰ ነው?”

© The Bible Society of Ethiopia, 2005

© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997

Bible Society of Ethiopia
跟着我们:



广告