Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




ዘኍል 16:32 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

32 ምድ​ሪ​ቱም አፍ​ዋን ከፍታ እነ​ር​ሱን፥ ቤተ ሰቦ​ቻ​ቸ​ው​ንም፥ ለቆ​ሬም የነ​በ​ሩ​ትን ሰዎች ሁሉ፥ ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ዋጠ​ቻ​ቸው።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

32 አፏንም ከፍታ ሰዎቹን ከነቤተ ሰቦቻቸው እንዲሁም የቆሬን ሰዎች በሙሉ፣ ንብረታቸውንም ሁሉ ዋጠች።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

32 ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ እነርሱን ቤተ ሰቦቻቸውንም፥ የቆሬም የሆኑትን ሰዎች ሁሉ፥ ዕቃዎቻቸውንም ሁሉ ዋጠቻቸው።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

32 እነርሱንና ቤተሰቦቻቸውን፥ የቆሬን ተከታዮችና ያላቸውን ንብረት ሁሉ ዋጠች።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

32 ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ እነርሱን ቤተ ሰቦቻቸውንም፥ ለቆሬም የነበሩትን ሰዎች ሁሉ፥ ዕቃዎቻቸውንም ሁሉ ዋጠቻቸው።

Ver Capítulo Cópia de




ዘኍል 16:32
21 Referências Cruzadas  

አሁ​ንም የወ​ን​ድ​ም​ህን ደም ከእ​ጅህ ለመ​ቀ​በል አፍ​ዋን በከ​ፈ​ተች በም​ድር ላይ አንተ የተ​ረ​ገ​ምህ ነህ።


የቀ​ዓት ልጆች፤ ልጁ አሚ​ና​ዳብ፥ ልጁ ቆሬ፥ ልጁ አሴር፤


የታ​ሐት ልጅ፥ የአ​ሴር ልጅ፥ የአ​ብ​ያ​ሳፍ ልጅ፥ የቆሬ ልጅ፥


ከበ​ደ​ላ​ቸው ጎዳና ተቀ​በ​ላ​ቸው፥ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ተሠ​ቃ​ይ​ተ​ዋ​ልና።


አቤቱ፥ ስም​ህን አመ​ሰ​ግን ዘንድ ሰው​ነ​ቴን ከእ​ሥ​ራት አው​ጣት፤ ዋጋ​ዬን እስ​ክ​ት​ሰ​ጠኝ ድረስ ጻድ​ቃን እኔን ይጠ​ብ​ቃሉ።


አቤቱ፦ ምድ​ር​ህን ይቅር አልኽ። የያ​ዕ​ቆ​ብ​ንም ምርኮ መለ​ስህ።


አቤቱ፥ ጆሮ​ህን ወደ እኔ አዘ​ን​ብል ስማ​ኝም፥ ድሃና ምስ​ኪን ነኝና።


አቤቱ፥ ምሕ​ረ​ት​ህን ለዘ​ለ​ዓ​ለም እዘ​ም​ራ​ለሁ። ጽድ​ቅ​ህ​ንም በአፌ ለልጅ ልጅ እና​ገ​ራ​ለሁ።


ምድር ደነ​ገ​ጠች፤ ታወ​ከ​ችም፤ ምድር ጐሰ​ቈ​ለች፤ ተነ​ዋ​ወ​ጠ​ችም።


ሲኦ​ልም ሆድ​ዋን አስ​ፍ​ታ​ለች፤ አፍ​ዋ​ንም ያለ ልክ ከፍ​ታ​ለች፤ የተ​ከ​በ​ሩና ታላ​ላቅ ሰዎች ባለ​ጠ​ጎ​ቻ​ቸ​ውና ድሆ​ቻ​ቸ​ውም ወደ እር​ስዋ ይወ​ር​ዳሉ።


ሁላ​ች​ሁም ጥና​ዎ​ቻ​ች​ሁን ውሰዱ፤ ዕጣ​ንም አድ​ር​ጉ​ባ​ቸው፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ች​ሁም ሁለት መቶ አምሳ ጥና​ዎ​ቻ​ች​ሁን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አምጡ፤ አንተ ደግሞ አሮ​ንም ጥና​ዎ​ቻ​ች​ሁን አምጡ” አለው።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን አዲስ ነገር ቢፈ​ጥር፥ ምድ​ርም አፍ​ዋን ከፍታ እነ​ር​ሱን፥ ቤታ​ቸ​ውን፥ ድን​ኳ​ና​ቸ​ውን፥ ለእ​ነ​ር​ሱም ያለ​ውን ሁሉ ብት​ው​ጣ​ቸው፥ በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸ​ውም ወደ ሲኦል ቢወ​ርዱ፥ ያን​ጊዜ እነ​ዚህ ሰዎች እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እንደ አስ​ቈጡ ታው​ቃ​ላ​ቸሁ።”


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ ይህን ቃል ሁሉ መና​ገር በፈ​ጸመ ጊዜ ከበ​ታ​ቻ​ቸው ያለ​ችው መሬት ተሰ​ነ​ጠ​ቀች፤


እነ​ር​ሱም፥ ለእ​ነ​ር​ሱም የነ​በሩ ሁሉ በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው ወደ ሲኦል ወረዱ፤ ምድ​ሪ​ቱም ተዘ​ጋ​ች​ባ​ቸው፤ ከማ​ኅ​በ​ሩም መካ​ከል ጠፉ።


በቆ​ሬም ምክ​ን​ያት ከሞ​ቱት ሌላ በመ​ቅ​ሠ​ፍቱ የሞ​ቱት ዐሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ነበሩ።


ማኅ​በ​ሩም በሞቱ ጊዜ ምድ​ሪቱ አፍ​ዋን ከፍታ ከቆሬ ጋር ዋጠ​ቻ​ቸው፤ በዚ​ያም ጊዜ እሳ​ቲቱ ሁለት መቶ አም​ሳ​ውን ሰዎች አቃ​ጠ​ለ​ቻ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም ለም​ል​ክት ሆኑ።


የቆሬ ልጆች ግን አል​ሞ​ቱም።


“አባ​ታ​ችን በም​ድረ በዳ ሞተ፤ በራሱ ኀጢ​አት ሞተ እንጂ ከቆሬ ጋር በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላይ በተ​ሰ​በ​ሰቡ ወገን መካ​ከል አል​ነ​በ​ረም፤ ወን​ዶ​ችም ልጆች አል​ነ​በ​ሩ​ትም።


“የቀ​ዓ​ትን ወገ​ኖች ነገድ ከሌ​ዋ​ው​ያን መካ​ከል አታ​ጥ​ፉ​አ​ቸው፤


በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ መካ​ከል ምድር አፍ​ዋን ከፍታ እነ​ር​ሱ​ንና ቤተ ሰቦ​ቻ​ቸ​ውን፥ ድን​ኳ​ኖ​ቻ​ቸ​ው​ንም፥ ለእ​ነ​ር​ሱም የነ​በ​ራ​ቸ​ውን ሁሉ በዋ​ጠ​ቻ​ቸው በሮ​ቤል ልጅ በኤ​ል​ያብ ልጆች በዳ​ታ​ንና በአ​ቤ​ሮን ያደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ፤


ምድሪቱም ሴቲቱን ረዳቻት፤ ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠችው።


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios