Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




መሳፍንት 13:16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

16 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መል​አክ ማኑ​ሄን፥ “አንተ የግድ ብት​ለኝ እህ​ል​ህን አል​በ​ላም፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት ብታ​ደ​ርግ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቅ​ር​በው” አለው። ማኑ​ሄም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ መሆ​ኑን አላ​ወ​ቀም ነበር።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

16 የእግዚአብሔርም መልአክ ማኑሄን፣ “የግድ ብታቈየኝ እንኳ የምታቀርበውን ማንኛውንም ምግብ አልበላም፤ ነገር ግን የሚቃጠል መሥዋዕት የምታዘጋጅ ከሆነ እርሱን ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። የሚያነጋግረው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

16 የጌታም መልአክ፥ “የግድ ብታቈየኝ እንኳ የምታቀርበውን ማንኛውንም ምግብ አልበላም፤ ነገር ግን የሚቃጠል መሥዋዕት የምታዘጋጅ ከሆነ እርሱን ለጌታ አቅርበው” አለው። የሚያነጋግረው የጌታ መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

16 የእግዚአብሔርም መልአክ ማኑሄን “ምንም አንተ ብታቈየኝ ምግብህን አልበላም፤ የሚቃጠል መሥዋዕት ማዘጋጀት ብትፈልግ ግን ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። ማኑሄ የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

16 የእግዚአብሔርም መልአክ ማኑሄን፦ አንተ የግድ ብትለኝ መብልህን አልበላም፥ የሚቃጠለውንም መሥዋዕት ማዘጋጀት ብትወድድ ለእግዚአብሔር አቅርበው አለው። ማኑሄም የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

Ver Capítulo Cópia de




መሳፍንት 13:16
5 Referências Cruzadas  

ከዛ​ፉም ሥር ዕረፉ፤ እን​ጀ​ራም እና​ም​ጣ​ላ​ች​ሁና ብሉ፤ ከዚ​ያም በባ​ሪ​ያ​ችሁ ዘንድ ከአ​ረ​ፋ​ችሁ በኋላ፥ ወደ ዐሰ​ባ​ች​ሁት ትሄ​ዳ​ላ​ችሁ።” እነ​ር​ሱም፥ “እን​ዳ​ልህ እን​ዲሁ አድ​ርግ” አሉት።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መል​አክ ዳግ​መኛ ለማ​ኑ​ሄና ለሚ​ስቱ አል​ተ​ገ​ለ​ጠም፤ ያን ጊዜም ማኑሄ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ መሆ​ኑን ዐወቀ።


ሚስ​ቱም፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርስ ሊገ​ድ​ለን ቢወ​ድድ ኖሮ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የእ​ህ​ሉን ቍር​ባን ከእ​ጃ​ችን ባል​ተ​ቀ​በ​ለን፥ ይህ​ንም ነገር ሁሉ ባላ​ሳ​የን፥ እን​ዲህ ያለ ነገ​ርም በዚህ ጊዜ ባላ​ሰ​ማን ነበር” አለ​ችው።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መል​አክ፥ “ሥጋ​ው​ንና የቂ​ጣ​ውን እን​ጎቻ ወስ​ደህ በዚህ ድን​ጋይ ላይ አኑር፤ መረ​ቁ​ንም አፍ​ስስ” አለው። እን​ዲ​ሁም አደ​ረገ።


በዚ​ያም ተራራ አናት ላይ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ አሳ​ም​ረህ ሥራ፤ ሁለ​ተ​ኛ​ዉ​ንም በሬ ውሰድ፤ በዚ​ያም በቈ​ረ​ጥ​ኸው በማ​ም​ለ​ኪያ ዐጸዱ እን​ጨት ላይ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት አቅ​ርብ” አለው።


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios