Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




ኤርምያስ 31:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

14 የካ​ህ​ና​ቱ​ንም የሌ​ዊን ልጆች ሰው​ነት ከፍ ከፍ አደ​ር​ጋ​ታ​ለሁ፤ አረ​ካ​ታ​ለሁ፤ ሕዝ​ቤም ከበ​ረ​ከቴ ይጠ​ግ​ባል፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

14 ካህናቱን አትረፍርፌ እባርካለሁ፤ ሕዝቤም በልግስናዬ ይጠግባል፤” ይላል እግዚአብሔር።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

14 የካህናቱንም ነፍስ በብዛት አረካታለሁ ሕዝቤም በጎነቴን ይጠግባል፥ ይላል ጌታ።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

14 ካህናቱን በምድሪቱ በረከት አጠግባቸዋለሁ፤ ለሕዝቤም ቸርነቴን አትረፈርፍላቸዋለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ይህን ተናግሬአለሁ።”

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

14 የካህናቱንም ነፍስ በብዛት አረካታለሁ ሕዝቤም በጎነቴን ይጠግባል።

Ver Capítulo Cópia de




ኤርምያስ 31:14
32 Referências Cruzadas  

አሁ​ንም አቤቱ አም​ላክ ሆይ፥ ከኀ​ይ​ልህ ታቦት ጋር ወደ ዕረ​ፍ​ትህ ተነሣ፤ አቤቱ አም​ላክ ሆይ፥ ካህ​ና​ትህ ደኅ​ን​ነ​ትን ይል​በሱ፤ ቅዱ​ሳ​ን​ህም በደ​ስታ ደስ ይበ​ላ​ቸው።


የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆ​ችና የሌዊ ልጆ​ችም የእ​ህ​ሉ​ንና የወ​ይ​ኑን፥ የዘ​ይ​ቱ​ንም ቀዳ​ም​ያት፥ የመ​ቅ​ደ​ሱን ዕቃ​ዎ​ችና የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሉት ካህ​ናት፥ በረ​ኞ​ቹና መዘ​ም​ራኑ ወዳ​ሉ​ባ​ቸው ጓዳ​ዎች ያግ​ቡት፤ እን​ዲ​ሁም የአ​ም​ላ​ካ​ች​ንን ቤት ከቶ አን​ተ​ውም።


ካህን ሞዓ​ብም ተስ​ፋዬ ነው፥ በኤ​ዶ​ም​ያስ ላይም ጫማ​ዬን እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ምም ይገ​ዙ​ል​ኛል።


አቤቱ፥ ከተ​ግ​ሣ​ጽህ፥ ከመ​ዓ​ት​ህም መን​ፈስ እስ​ት​ን​ፋስ የተ​ነሣ፥ የው​ኆች ምን​ጮች ታዩ፥ የዓ​ለም መሠ​ረ​ቶ​ችም ተገ​ለጡ።


መዓ​ትን ተዋት፤ ቍጣ​ንም ጣላት፥ እን​ዳ​ት​በ​ድ​ልም አት​ቅና።


ከክ​ፉ​ዎች ሴራ ከብ​ዙ​ዎች ዐመፅ አድ​ራ​ጊ​ዎች ሰው​ረኝ።


ለእ​ነ​ርሱ ለራ​ሳ​ቸው ክፉ ነገ​ርን አጸኑ፤ ወጥ​መ​ድን ይሰ​ውሩ ዘንድ ተማ​ከሩ፤ የሚ​ያ​ም​ንም የለም ይላሉ።


ዐመ​ፃን ፈለ​ጓት፥ ሲፈ​ት​ኑም ሲጀ​ም​ሩም አለቁ፤ ሰው በጥ​ልቅ ልብ ውስጥ ይገ​ባል፥


ምድር ሁላ ለአ​ንተ ትሰ​ግ​ዳ​ለች፥ ለአ​ን​ተም ትገ​ዛ​ለች፥ ለስ​ም​ህም ትዘ​ም​ራ​ለች።


ምሕ​ረ​ትህ በእኔ ላይ ታላቅ ናትና፥ ነፍ​ሴ​ንም ከታ​ች​ኛ​ዪቱ ሲኦል አድ​ነ​ሃ​ታ​ልና።


በእኔ ተማ​ም​ኖ​አ​ልና አድ​ነ​ዋ​ለሁ ስሜ​ንም አው​ቆ​አ​ልና እጋ​ር​ደ​ዋ​ለሁ።


እኅቴ ሙሽ​ሪት ሆይ፥ ወደ ገነቴ ገባሁ፥ ከር​ቤ​ዬን ከሽ​ቱዬ ጋር ለቀ​ምሁ፥ እን​ጀ​ራ​ዬን ከማሬ ጋር በላሁ፥ የወ​ይን ጠጄን ከወ​ተቴ ጋር ጠጣሁ። ባል​ን​ጀ​ሮች በሉ፥ ጠገ​ቡም፤ የወ​ን​ድ​ሞች ልጆች ጠጡ፥ ሰከ​ሩም፥ ልባ​ቸው የጠፋ ነውና።


የሠ​ራ​ዊት ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለሕ​ዝቡ ሁሉ ግብ​ዣን ያደ​ር​ጋል፤ በዚህ ተራራ ላይ ሐሤ​ትን ያደ​ር​ጋሉ፤ የወ​ይን ጠጅ​ንም ይጠ​ጣሉ፤ ዘይ​ት​ንም ይቀ​ባሉ።


እና​ንተ ግን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ካህ​ናት ትባ​ላ​ላ​ችሁ፤ የአ​ም​ላ​ካ​ች​ንም አገ​ል​ጋ​ዮች ተብ​ላ​ችሁ ትጠ​ራ​ላ​ችሁ፤ የአ​ሕ​ዛ​ብን ሀብት ትበ​ላ​ላ​ችሁ፤ በሀ​ብ​ታ​ቸ​ውም ትመ​ካ​ላ​ችሁ።


የተ​ጠ​ማ​ች​ውን ነፍስ ሁሉ አር​ክ​ቻ​ለ​ሁና፥ የተ​ራ​በ​ች​ው​ንም ነፍስ ሁሉ አጥ​ግ​ቤ​አ​ለ​ሁና።


ይህ​ችም ከተማ እኔ የም​ሠ​ራ​ላ​ቸ​ውን በጎ​ነት ሁሉ በሚ​ሰሙ፥ እኔም ስላ​መ​ጣ​ሁ​ላ​ቸው በጎ​ነ​ትና ሰላም ሁሉ በሚ​ፈ​ሩና በሚ​ደ​ነ​ግጡ አሕ​ዛብ ሁሉ ፊት ለደ​ስታ፥ ለክ​ብ​ርና ለገ​ና​ን​ነት ትሆ​ና​ለች።”


እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ወደ ማሰ​ማ​ር​ያው እመ​ል​ሳ​ለሁ፥ በቀ​ር​ሜ​ሎ​ስና በባ​ሳን፥ በኤ​ፍ​ሬም ተራ​ራና በገ​ለ​ዓ​ድም ይሰ​ማ​ራል፤ ነፍ​ሱም ትጠ​ግ​ባ​ለች።


በመ​ል​ካም ማሰ​ማ​ርያ አስ​ማ​ራ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ጕረ​ኖ​አ​ቸ​ውም በረ​ዥ​ሞቹ በእ​ስ​ራ​ኤል ተራ​ሮች ላይ ይሆ​ናል፤ በዚያ በመ​ል​ካም ጕረኖ ውስጥ ይመ​ሰ​ጋሉ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ተራ​ሮች ላይ በለ​መ​ለመ ማሰ​ማ​ርያ ይሰ​ማ​ራሉ።


ዘር በጎተራ ገና ይኖራልን? ወይንና በለስ ሮማንና ወይራ አላፈሩም፣ ከዚህች ቀን ጀምሬ እባርካችኋለሁ።


ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፤ይጠግባሉና።


በክ​ር​ስ​ቶስ ኢየ​ሱስ በሰ​ማ​ያዊ ስፍራ በመ​ን​ፈ​ሳዊ በረ​ከት ሁሉ የባ​ረ​ከን የጌ​ታ​ችን የኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶስ አባት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይመ​ስ​ገን።


የክ​ር​ስ​ቶ​ስን ፍቅር ለመ​ረ​ዳት፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍጹ​ም​ነት በሁሉ ፍጹ​ማን ትሆኑ ዘንድ።


ስለ ንፍ​ታ​ሌ​ምም እን​ዲህ አለ፦ ንፍ​ታ​ሌም ከበጎ ነገር ጠግ​ቦ​አል፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በረ​ከት ተሞ​ል​ቶ​አል፤ ባሕ​ር​ንና ሊባን ይወ​ር​ሳል።


እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios