Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




ዘፀአት 14:13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

13 ሙሴም ለሕ​ዝቡ፥ “አት​ፍሩ፤ ዛሬ የም​ታ​ዩ​አ​ቸ​ውን ግብ​ፃ​ው​ያ​ንን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አታ​ዩ​አ​ቸ​ው​ምና ቁሙ፤ ዛሬ ለእ​ና​ንተ የሚ​ያ​ደ​ር​ጋ​ትን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ማዳን እዩ።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

13 ሙሴም ለሕዝቡ መለሰላቸው፤ “አትሸበሩ፣ ጸንታችሁ ቁሙ፤ እግዚአብሔር ዛሬ የሚያደርግላችሁን መታደግ ታያላችሁ፤ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብጻውያንን ዳግም አታዩአቸውም።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

13 ሙሴም ሕዝቡን እንዲህ አላቸው፦ “አትፍሩ፥ ቁሙ፥ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የጌታን ማዳን እዩ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘለዓለም አታዩአቸውምና።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

13 ሙሴም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦ “አይዞአችሁ አትፍሩ! ባላችሁበት ጸንታችሁ ቁሙ፤ እግዚአብሔር እናንተን ለማዳን የሚያደርገውን ዛሬ ታያላችሁ፤ እነዚህን ዛሬ የምታዩአቸውን ግብጻውያን ዳግመኛ አታዩአቸውም።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

13 ሙሴም ለሕዝቡ፦ “አትፍሩ፤ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘላለም አታዩአቸውምና ቁሙ፤ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ።

Ver Capítulo Cópia de




ዘፀአት 14:13
36 Referências Cruzadas  

ከዚ​ህም ነገር በኋላ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በራ​እይ ወደ አብ​ራም መጣ፤ እን​ዲህ ሲል፥ “አብ​ራም ሆይ፥ አት​ፍራ፤ እኔ ጋሻ እሆ​ን​ሃ​ለሁ፤ ዋጋ​ህም በእኔ ዘንድ እጅግ ብዙ ነው።”


በዚ​ያ​ችም ሌሊት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተገ​ለ​ጠ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አለው፥ “እኔ የአ​ባ​ትህ የአ​ብ​ር​ሃም አም​ላክ ነኝ፤ አት​ፍራ፤ እኔ ከአ​ንተ ጋር ነኝና፤ እባ​ር​ክ​ሃ​ለሁ፤ ስለ አባ​ትህ ስለ አብ​ር​ሃም ዘር​ህን አበ​ዛ​ዋ​ለሁ።”


አለ​ውም፥ “የአ​ባ​ቶ​ችህ አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እኔ ነኝ፤ ወደ ግብፅ መው​ረ​ድን አት​ፍራ፤ በዚያ ትልቅ ሕዝብ አደ​ር​ግ​ሃ​ለ​ሁና።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያድ​ነው ዘንድ ይጠ​ብ​ቃል።


እር​ሱም፥ “ከእኛ ጋር ያሉት ከእ​ነ​ርሱ ጋር ካሉት ይበ​ል​ጣ​ሉና አት​ፍራ” አለው።


በእ​ር​ሻ​ውም መካ​ከል ቆመው ጠበ​ቁት፥ ያች​ንም ቦታ አዳ​ናት፤ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ን​ንም ገደ​ላ​ቸው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በታ​ላቅ ማዳን አዳ​ና​ቸው።


እን​ዲ​ህም አለ፥ “ይሁዳ ሁሉ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም የም​ት​ኖሩ፥ አን​ተም ንጉሡ ኢዮ​ሣ​ፍጥ! ስሙ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ች​ኋል፦ ሰልፉ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው እንጂ የእ​ና​ንተ አይ​ደ​ለ​ምና ከዚህ ታላቅ ወገን የተ​ነሣ አት​ፍሩ፤ አት​ደ​ን​ግ​ጡም።


እና​ንተ የም​ቷጉ አይ​ደ​ላ​ች​ሁም፤ ይሁ​ዳና ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ፥ ተሰ​ለፉ፤ ዝም ብላ​ችሁ ቁሙ፤ የሚ​ሆ​ነ​ው​ንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ማዳን እዩ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከእ​ና​ንተ ጋር ነውና አት​ፍሩ፤ አት​ደ​ን​ግ​ጡም፤ ነገም ውጡ​ባ​ቸው።”


“በግ​ብ​ጽም ሳሉ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ንን መከራ አየህ፤ በኤ​ር​ትራ ባሕ​ርም ሳሉ ጩኸ​ታ​ቸ​ውን ሰማህ፤


ማዳን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፥ በረ​ከ​ት​ህም በሕ​ዝ​ብህ ላይ ነው።


በመ​ብሌ ውስጥ ሐሞ​ትን ጨመሩ፥ ለጥ​ማ​ቴም ሆም​ጣ​ጤን አጠ​ጡኝ።


አቤቱ፥ አንተ ግን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ልዑል ነህ፤


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዚያ ቀን እስ​ራ​ኤ​ልን ከግ​ብ​ፃ​ው​ያን እጅ አዳ​ና​ቸው፤ እስ​ራ​ኤ​ልም ግብ​ፃ​ው​ያን እንደ ሞቱ በባ​ሕር ዳር አዩ።


ሙሴም ለሕ​ዝቡ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሊፈ​ት​ና​ችሁ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም እን​ዳ​ት​ሠሩ እር​ሱን መፍ​ራት በእ​ና​ንተ ያድር ዘንድ መጥ​ቶ​አ​ልና አት​ፍሩ” አላ​ቸው።


በአ​ንተ ላይ ታም​ና​ለ​ችና በአ​ንተ የም​ት​ደ​ገፍ ነፍ​ስን ፈጽ​መህ በሰ​ላም ትጠ​ብ​ቃ​ታ​ለህ።


የእ​ስ​ራ​ኤል ቅዱስ፥ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ልና፥ “ብት​ጸ​ጸ​ትና ብታ​ለ​ቅስ ትድ​ና​ለህ፤ የት እን​ዳ​ለ​ህም ታው​ቃ​ለህ፤ በከ​ንቱ ታም​ነ​ሃ​ልና፤ ኀይ​ላ​ች​ሁም ከንቱ ይሆ​ናል፤ እና​ንተ ግን መስ​ማ​ትን እንቢ አላ​ችሁ፤


እና​ንተ አእ​ምሮ የሌ​ላ​ችሁ፥ ልቡ​ና​ች​ሁን አረ​ጋጉ፤ ጽኑ፤ አት​ፍሩ፤ እነሆ፥ አም​ላ​ካ​ችን ፍር​ድን ይመ​ል​ሳል፤ ይበ​ቀ​ላ​ልም፤ እር​ሱም መጥቶ ያድ​ነ​ናል።


እኔ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ፤ ከእኔ ሌላ የሚ​ያ​ድን አም​ላክ የለም።


እን​ዲ​ህም በለው፥ “ተጠ​በቅ፥ ዝምም በል፤ አት​ፍራ፤ ከእ​ነ​ዚህ ከሚ​ጤሱ ሁለት የእ​ን​ጨት ጠለ​ሸ​ቶች፥ የተ​ነሣ ልብህ አይ​ደ​ን​ግጥ፤ ከተ​ቈ​ጣሁ በኋላ ይቅር እላ​ለ​ሁና።


በእ​ው​ነት የተ​ራ​ሮች ኀይል፥ የኮ​ረ​ብ​ቶ​ችም ኀይል ሐሰት ነው፤ ነገር ግን የእ​ስ​ራ​ኤል መዳን በአ​ም​ላ​ካ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ነው።


ለም​ት​ሻ​ውና ለም​ት​ታ​ገሥ፥ ዝም ብላም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ማዳን ተስፋ ለም​ታ​ደ​ርግ ነፍስ መል​ካም ነው።


ነገር ግን የይ​ሁ​ዳን ልጆች ይቅር እላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እኔ አም​ላ​ካ​ቸ​ውም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አድ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ እንጂ በቀ​ስት ወይም በሰ​ይፍ፥ ወይም በጦር፥ ወይም በሠ​ረ​ገላ፥ ወይም በፈ​ረ​ሶች፥ ወይም በፈ​ረ​ሰ​ኞች የማ​ድ​ና​ቸው አይ​ደ​ለም” አለው።


ሰማ​ይን ያጸ​ናሁ፥ ምድ​ር​ንም የፈ​ጠ​ርሁ፥ እጆ​ችም የሰ​ማይ ሠራ​ዊ​ትን ያቆሙ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እኔ ነኝ። እን​ዳ​ት​ከ​ተ​ላ​ቸ​ውም እነ​ር​ሱን አላ​ሳ​የ​ሁ​ህም። ከግ​ብፅ ምድ​ርም ያወ​ጣ​ሁህ እኔ ነኝ። ከእኔ በቀር ሌላ አም​ላክ አት​ወቅ፤ ከእኔ በቀር የሚ​ያ​ድ​ንህ የለ​ምና።


እስ​ራ​ኤል ሆይ! በመ​ከ​ራህ ጊዜ ማን ይረ​ዳ​ሃል?


ሕዝብህን ለመታደግ፥ የቀባኸውንም ለማዳን ወጣህ፣ የኃጢአተኛውን ቤት ራስ ቀጠቀጥህ፣ መሠረቱን እስከ አንገቱ ድረስ ገለጥህ።


በውኑ እግዚአብሔር በወንዞች ላይ ተቈጥቶአልን? ቍጣህ በወንዞች ላይ፥ መዓትህም በባሕር ላይ ነውን? በፈረሶችህና በማዳንህ ሰረገሎች ላይ ተቀምጠሃልና።


ነገር ግን እና​ንተ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላይ አታ​ምፁ፤ እኛ እና​ጠ​ፋ​ቸ​ዋ​ለ​ንና የም​ድ​ሪ​ቱን ሰዎች አት​ፍሩ፤ ጊዜ​አ​ቸው አል​ፎ​ባ​ቸ​ዋል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከእኛ ጋር ነው፤ አት​ፍ​ሩ​አ​ቸው” ብለው ተና​ገ​ሩ​አ​ቸው።


መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው “እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና፤


እስ​ራ​ኤል ሆይ፥ ስማ፤ ዛሬ ጠላ​ቶ​ቻ​ች​ሁን ለመ​ው​ጋት ትሄ​ዳ​ላ​ችሁ፤ ልባ​ችሁ አይ​ታ​ወክ፤ አት​ፍሩ፤ አት​ሸ​በሩ፤ ከፊ​ታ​ቸ​ውም ፈቀቅ አት​በሉ፤


ሳኦ​ልም፦“በዚ​ያች ቀን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለእ​ስ​ራ​ኤል ድኅ​ነ​ትን አድ​ር​ጎ​አ​ልና ዛሬ አንድ ሰው አይ​ሞ​ትም” አለ።


አሁ​ንም ቁሙ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዐ​ይ​ና​ችሁ ፊት የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን ይህን ታላቅ ነገር ተመ​ል​ከቱ።


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios