Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




2 ሳሙኤል 13:4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

4 እር​ሱም፥ “የን​ጉሥ ልጅ ሆይ፥ ስለ​ምን በየ​ቀኑ እን​ዲህ ከሳህ? አት​ነ​ግ​ረ​ኝ​ምን?” አለው። አም​ኖ​ንም፥ “የወ​ን​ድ​ሜን የአ​ቤ​ሴ​ሎ​ምን እኅት ትዕ​ማ​ርን እወ​ድ​ዳ​ታ​ለሁ” አለው።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

4 አምኖንንም፣ “የንጉሥ ልጅ ሆይ፤ ሰውነትህ ቀን በቀን የሚከሳበትን ምክንያት ለምን አትነግረኝም?” ሲል ጠየቀው። አምኖንም፣ “የወንድሜን የአቤሴሎምን እኅት ትዕማርን አፍቅሬ ነው” አለው።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

4 እርሱም አምኖንን፥ “የንጉሥ ልጅ ሆይ፤ ሰውነትህ ቀን በቀን የሚከሳው ለምንድነው? ለምን አትነግረኝም?” ሲል ጠየቀው። አምኖንም፥ “የወንድሜን የአቤሴሎምን እኅት ትዕማርን አፍቅሬ ነው” አለው።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

4 ዮናዳብ አምኖንን “አንተ የንጉሥ ልጅ ሆነህ ሳለ በየቀኑ ሰውነትህ ጠውልጎ የማይህ ስለምንድን ነው? እስቲ ንገረኝ” ሲል ጠየቀው። አምኖንም “የወንድሜን የአቤሴሎምን እኅት ትዕማርን ስለ ወደድኩ ነው” ሲል መለሰለት።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

4 እርሱም፦ የንጉሥ ልጅ ሆይ፥ ስለ ምን ቀን በቀን እንዲህ ከሳህ? አትነግረኝምን? አለው። አምኖንም፦ የወንድሜን የአቤሴሎምን እኅት ትዕማርን እወድዳታለሁ አለው።

Ver Capítulo Cópia de




2 ሳሙኤል 13:4
11 Referências Cruzadas  

ለአ​ም​ኖ​ንም የዳ​ዊት ወን​ድም የሳ​ምዓ ልጅ ኢዮ​ና​ዳብ የሚ​ባል ወዳጅ ነበ​ረው፤ ኢዮ​ና​ዳ​ብም እጅግ ብልህ ሰው ነበረ።


ኢዮ​ና​ዳ​ብም አለው፦“ ታም​ሜ​አ​ለሁ ብለህ በአ​ል​ጋህ ላይ ተኛ፤ አባ​ት​ህም ሊያ​ይህ ይመ​ጣል፦ እኅቴ ትዕ​ማር እን​ድ​ት​መ​ጣና እኔ የም​በ​ላ​ውን እን​ጀራ እን​ድ​ት​ሰ​ጠኝ፥ መብ​ሉ​ንም እኔ እያ​የሁ እን​ድ​ታ​በ​ስ​ል​ልኝ፥ ከእ​ጅ​ዋም እን​ድ​በ​ላው እለ​ም​ን​ሃ​ለሁ በለው።”


ደግ​ሞም መል​እ​ክ​ተ​ኞች ተመ​ል​ሰው መጥ​ተው እን​ዲህ አሉት፥ “ወልደ አዴር እን​ዲህ ይላል፦ ቀድ​መህ ብር​ህ​ንና ወር​ቅ​ህን፥ ሚስ​ቶ​ች​ህ​ንና ልጆ​ች​ህ​ንም ላክ​ልኝ ብዬ ልኬ​ብህ ነበር፤


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ የሀ​ገ​ሩን አለ​ቆች ሁሉ ጠርቶ፥ “ተመ​ል​ከቱ፤ ይህም ሰው ክፉ እን​ዲሻ እዩ፤ ስለ ሚስ​ቶቼ ስለ ወን​ዶች ልጆ​ቼና ሴቶች ልጆቼ ላከ​ብኝ፤ ብሬ​ንና ወር​ቄን ግን አል​ከ​ለ​ከ​ል​ሁ​ትም” አላ​ቸው።


ዛሬም ክብ​ራ​ቸው ተዋ​ር​ዷ​ልና፥ ፊታ​ቸ​ውም አፍ​ሯ​ልና ኀጢ​አ​ታ​ቸው እንደ ሰዶ​ምና እንደ ገሞራ ኀጢ​አት ተቃ​ወ​መ​ቻ​ቸው፤ በላ​ያ​ቸ​ውም ተገ​ልጣ ታወ​ቀች።


አስ​ጸ​ያፊ ነገ​ርን ስለ ሠሩ አፍ​ረ​ዋ​ልን? ምንም አላ​ፈ​ሩም፤ እፍ​ረ​ት​ንም አላ​ወ​ቁም፤ ስለ​ዚህ ከሚ​ወ​ድቁ ጋር ይወ​ድ​ቃሉ፤ በጐ​በ​ኘ​ኋ​ቸ​ውም ጊዜ ይዋ​ረ​ዳሉ፤ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


የእ​ኅ​ት​ህን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ባ​ትህ ልጅ ወይም የእ​ና​ትህ ልጅ በቤት ወይም በውጭ የተ​ወ​ለ​ደች ብት​ሆን፥ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን አት​ግ​ለጥ።


“ማና​ቸ​ውም ሰው የአ​ባ​ቱን ልጅ ወይም የእ​ና​ቱን ልጅ እኅ​ቱን ቢያ​ገባ፥ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋ​ንም ቢያይ፥ እር​ስ​ዋም ኀፍ​ረተ ሥጋ​ውን ብታይ፥ ይህ ጸያፍ ነገር ነው፤ በሕ​ዝ​ባ​ቸ​ውም ልጆች ፊት ይገ​ደሉ፤ የእ​ኅ​ቱን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አ​ልና ኀጢ​አ​ቱን ይሸ​ከ​ማል።


እጆቻቸውን ለክፋት ያነሣሉ፥ አለቃውና ፈራጁ ጉቦን ይፈልጋሉ፥ ትልቁም ሰው እንደ ነፍሱ ምኞት ይናገራል፥ እንዲሁም ክፋትን ይጐነጕናሉ።


“አንተ ታናሽ መንጋ፥ አት​ፍራ፤ አባ​ታ​ችሁ መን​ግ​ሥ​ቱን ሊሰ​ጣ​ችሁ ወዶ​አ​ልና።


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios