Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -




1 ቆሮንቶስ 1:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

12 እነሆ፥ እርስ በር​ሳ​ችሁ፥ “እኔ የጳ​ው​ሎስ ነኝ፤ እኔ የአ​ጵ​ሎስ ነኝ፤ እኔ የኬፋ ነኝ፤ እኔ የክ​ር​ስ​ቶስ ነኝ” የም​ት​ሉ​ትን እነ​ግ​ራ​ች​ኋ​ለሁ።

Ver Capítulo Cópia de

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

12 ነገሩም እንዲህ ነው፤ ከእናንተ አንዱ፣ “እኔ የጳውሎስ ነኝ” ሲል፣ ሌላው፣ “እኔ የአጵሎስ ነኝ” ይላል፤ ደግሞም አንዱ፣ “እኔ የኬፋ ነኝ” ሲል፣ ሌላው ደግሞ፣ “እኔስ የክርስቶስ ነኝ” ይላል።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

12 እኔ የምለው፥ እያንዳንዳችሁ “እኔ የጳውሎስ ነኝ፤” “እኔስ የአጵሎስ ነኝ፤” “እኔ ግን የኬፋ ነኝ፤” “እኔስ የክርስቶስ ነኝ፤” ትላላችሁ።

Ver Capítulo Cópia de

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

12 ይኸውም እናንተ እያንዳንዳችሁ “እኔ የጳውሎስ ነኝ፤ እኔ የአጵሎስ ነኝ፤ እኔ የጴጥሮስ ነኝ፤ እኔ የክርስቶስ ነኝ” ትላላችሁ።

Ver Capítulo Cópia de

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

12 ይህንም እላለሁ፦ እያንዳንዳችሁ፦ እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ።

Ver Capítulo Cópia de




1 ቆሮንቶስ 1:12
20 Referências Cruzadas  

በዚ​ያም ጊዜ የእ​ስ​ራ​ኤል ሕዝብ በሁ​ለት ተከ​ፈለ፤ የሕ​ዝ​ቡም እኩ​ሌታ የጎ​ና​ትን ልጅ ታም​ኒን ያነ​ግ​ሡት ዘንድ ተከ​ተ​ሉት፤ እኩ​ሌ​ቶ​ችም ዘን​በ​ሪን ተከ​ተሉ።


እናንተ ግን ‘መምህር’ ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።


እር​ሱም መጀ​መ​ሪያ ወን​ድሙ ስም​ዖ​ንን አግ​ኝቶ “በት​ር​ጓ​ሜው ክር​ስ​ቶስ የሚ​ሉት መሲ​ሕን አገ​ኘ​ነው” አለው።


በእ​ስ​ክ​ን​ድ​ር​ያም የሚ​ኖር፥ ንግ​ግር የሚ​ች​ልና መጽ​ሐ​ፍን የሚ​ያ​ውቅ አጵ​ሎስ የሚ​ባል አንድ አይ​ሁ​ዳዊ ሰው ወደ ኤፌ​ሶን መጣ።


ከዚ​ህም በኋላ አጵ​ሎስ በቆ​ሮ​ን​ቶስ ሳለ፥ ጳው​ሎስ ላይ ላዩን ሄዶ ወደ ኤፌ​ሶን መጣ፤ በዚ​ያም ጥቂት ደቀ መዛ​ሙ​ር​ትን አገኘ።


ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ሆይ! እን​ደ​ም​ት​ጣ​ሉና እን​ደ​ም​ት​ከ​ራ​ከሩ ከቀ​ሎ​ኤስ ወገ​ኖች ስለ እና​ንተ ነገ​ሩኝ።


ለጴ​ጥ​ሮስ ታየው፤ ከዚ​ህም በኋላ ለዐ​ሥራ አንዱ ደቀ መዛ​ሙ​ርቱ ታያ​ቸው።


ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ሆይ፥ ይህን እን​ነ​ግ​ራ​ች​ኋ​ለን፦ ሥጋ​ዊና ደማዊ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መን​ግ​ሥት አይ​ወ​ር​ስም፥ የሚ​ፈ​ር​ሰው የማ​ይ​ፈ​ር​ሰ​ውን አይ​ወ​ር​ስም።


ስለ ወን​ድ​ማ​ችን ስለ አጵ​ሎ​ስም ከወ​ን​ድ​ሞች ጋር ወደ እና​ንተ እን​ዲ​መጣ መላ​ልሼ ማል​ጄው ነበር፤ አሁን ሊመጣ አል​ወ​ደ​ደም፤ በተ​ቻ​ለው ጊዜ ግን ይመ​ጣል።


ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ሆይ! እኔም፥ አጵ​ሎ​ስም ብን​ሆን መከራ የተ​ቀ​በ​ል​ነው ስለ እና​ንተ ነው፤ እና​ንተ እን​ድ​ት​ማሩ፥ ከመ​ጻ​ሕ​ፍት ቃልም ወጥ​ታ​ችሁ በወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ችሁ ላይ እን​ዳ​ት​ታ​በዩ ነው።


ነገር ግን ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን እን​ዲህ ይቀ​ናል፤ የዚህ ዓለም ኑሮ ሁሉ ሊያ​ልፍ ቀር​ቦ​አ​ልና፤ አሁ​ንም ያገቡ እን​ዳ​ላ​ገቡ ይሆ​ናሉ።


እንደ ሌሎች ሐዋ​ር​ያት ሁሉና፥ እንደ ጌታ​ችን ወን​ድ​ሞች እንደ ኬፋም ከሴ​ቶች እኅ​ታ​ች​ንን ይዘን ልን​ዞር አይ​ገ​ባ​ን​ምን?


በፊ​ታ​ችሁ ያለ​ውን ተመ​ል​ከቱ፤ ማንም በክ​ር​ስ​ቶስ ያመነ ቢሆን፥ ይህን እንደ ገና በራሱ ይቍ​ጠ​ረው፤ እርሱ የክ​ር​ስ​ቶስ እንደ ሆነ እኛም እን​ዲሁ ነንና።


አሳ​ንሶ የሚ​ዘራ ለእ​ርሱ እን​ዲሁ መከሩ ያን​ስ​በ​ታል፤ በብዙ የሚ​ዘራ ግን በብዙ ያመ​ር​ታል።


የሰ​ጠ​ኝ​ንም ጸጋ ዐው​ቀው አዕ​ማድ የሚ​ሏ​ቸው ያዕ​ቆ​ብና ኬፋ፥ ዮሐ​ን​ስም እኛ ወደ አሕ​ዛብ፥ እነ​ር​ሱም ወደ አይ​ሁድ እን​ድ​ን​ሄድ ለእ​ኔና ለበ​ር​ና​ባስ ቀኝ እጃ​ቸ​ውን ሰጡን።


እን​ግ​ዲህ እን​ዲህ እላ​ለሁ፦ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ሰጠ ይህ ኪዳን ጽኑዕ ነው፤ ከዚ​ህም በኋላ በአ​ራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኦሪት መጣች፤ ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሰ​ጠ​ውን ተስፋ ልት​ከ​ለ​ክል አይ​ደ​ለም።


Siga-nos em:

Anúncios


Anúncios