Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


ኢዮብ 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የኢ​ዮብ መልስ

1 ኢዮ​ብም መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦

2 “ከእ​ና​ንተ አንዱ መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ምነው በመ​ዘነ ኖሮ! መከ​ራ​ዬ​ንም በአ​ን​ድ​ነት ምነው በሚ​ዛን ላይ ባኖ​ረው ኖሮ!

3 ከባ​ሕር አሸዋ ይልቅ ይከ​ብድ ነበ​ርና፤ ነገር ግን ቃሌ ሐሰ​ትን ይመ​ስ​ላል።

4 እነሆ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍላጻ በሥ​ጋዬ ላይ ነው፤ መር​ዙም ደሜን ይመ​ጥ​ጣል። ለመ​ና​ገር ስጀ​ም​ርም ይወ​ጋ​ኛል።

5 በውኑ የሜዳ አህያ ሣር እያ​ለው በከ​ንቱ ይጮ​ኻ​ልን? የሚ​በ​ላ​ውን ፈልጎ አይ​ደ​ለ​ምን? ወይስ በሬ በበ​ረት ውስጥ ገለባ ሳለው ይጮ​ኻ​ልን?

6 ምግብ ያለ ጨው ይበ​ላ​ልን? የጎ​መን ዘር ጭማ​ቂስ ይጣ​ፍ​ጣ​ልን? ወይስ ለከ​ንቱ ጣዕም አለ​ውን?

7 ሰው​ነቴ ማረፍ አል​ቻ​ለ​ችም፤ የሥ​ጋ​ዬን ክር​ፋት እንደ አን​በሳ ክር​ፋት እመ​ለ​ከ​ተ​ዋ​ለ​ሁና።

8 ልመ​ናዬ ምነው በደ​ረ​ሰ​ልኝ! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ተስ​ፋ​ዬን ምነው በሰ​ጠኝ!

9 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያቈ​ስ​ለኝ ዘንድ ጀመረ፥ ነገር ግን እስከ መጨ​ረ​ሻው አላ​ጠ​ፋ​ኝም።

10 መቃ​ብሬ በግ​ንቡ የም​መ​ላ​ለ​ስ​በት ከተ​ማዬ ይሁን፥ ከእ​ር​ሱም ፈቀቅ አል​ልም የአ​ም​ላ​ኬን ቅዱስ ቃል አል​ካ​ድ​ሁ​ምና።

11 እታ​ገሥ ዘንድ ጕል​በቴ ምን​ድን ነው? ነፍ​ሴም ትጽ​ናና ዘንድ ዘመኔ ምን​ድን ነው?

12 ጕል​በቴ የድ​ን​ጋይ ጉል​በት ነውን? በውኑ ሥጋ​ዬስ እንደ ናስ ነውን?

13 በእ​ርሱ የታ​መ​ንሁ አይ​ደ​ለ​ሁ​ምን? ረድ​ኤቱ ከእኔ ለምን ራቀ?

14 ምሕ​ረቱ ቸል አለኝ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አል​ጐ​በ​ኘ​ኝም አል​ተ​መ​ለ​ከ​ተ​ኝም።

15 “ወን​ድ​ሞ​ቼም እንደ ደረቅ ወንዝ፥ እንደ አለፈ ማዕ​በ​ልም አላ​ወ​ቁ​ኝም።

16 ያከ​ብ​ሩኝ የነ​በሩ እነ​ዚያ፥ አሁን እንደ በረ​ዶና እንደ ረጋ አመ​ዳይ ሆኑ​ብኝ፤

17 ወደ ሙቀት ሲቀ​ርብ በቀ​ለጠ ጊዜ ምን እንደ ነበረ አይ​ታ​ወ​ቅም።

18 እን​ደ​ዚ​ሁም እኔ ከሁሉ ተለ​ይቼ ጠፋሁ፥ ከቤ​ቴም ወጥቼ የተ​ጣ​ልሁ ሆንሁ።

19 የቴ​ማ​ና​ው​ያ​ንን መን​ገ​ዶች፥ የሳ​ባ​ው​ያ​ንን ክፋ​ትና ቸል​ተ​ኝ​ነት ተመ​ል​ከቱ።

20 በከ​ተ​ሞ​ችና በገ​ን​ዘ​ቦች የሚ​ታ​መኑ ያፍ​ራሉ።

21 አሁ​ንም እና​ንተ ያለ ምሕ​ረት መጣ​ችሁ፤ ቍስ​ሌ​ንም አይ​ታ​ችሁ ፈራ​ችሁ።

22 ለምን? በውኑ፦ ከእ​ና​ንተ አን​ዳች ነገር ጠየ​ቅ​ሁን? ወይስ፦ ከእ​ና​ንተ ኀይ​ልን ተመ​ኘ​ሁን?

23 ወይስ ከጠ​ላ​ቶች እጅ ታስ​ጥ​ሉኝ ዘንድ ከኀ​ይ​ለ​ኞ​ችም እጅ ታድ​ኑኝ ዘንድ።

24 “አስ​ተ​ም​ሩኝ፥ እኔም አዳ​ም​ጣ​ች​ኋ​ለሁ፤ የተ​ሳ​ሳ​ት​ሁ​ትም ካለ አስ​ረ​ዱኝ።

25 የእ​ው​ነ​ተኛ ሰው ቃል ሐሰ​ትን ይመ​ስ​ላል፥ ከእ​ና​ንተ ዘንድ ኀይ​ልን የም​ጠ​ይቅ አይ​ደ​ለ​ምና።

26 የን​ግ​ግ​ራ​ች​ሁም ማጽ​ና​ናት ዕረ​ፍ​ትን አይ​ሰ​ጠ​ኝም፤ የአ​ን​ደ​በ​ታ​ች​ሁም ቅል​ጥ​ፍና ደስ አያ​ሰ​ኘ​ኝም።

27 በድሃ አደጉ ላይ ትስ​ቃ​ላ​ች​ሁና፥ ወዳ​ጃ​ች​ሁ​ንም ትሰ​ድ​ባ​ላ​ች​ሁና።

28 አሁ​ንም፥ ፊታ​ች​ሁን አይቼ ሐሰት አል​ና​ገ​ርም።

29 አሁ​ንም ተቀ​መጡ፤ በደ​ልም አይ​ኑር፤ ዳግ​መ​ኛም ከጻ​ድቁ ጋር አንድ ሁኑ።

30 በአ​ን​ደ​በቴ በደል የለ​ምና አፌ ጕሮ​ሮ​ዬም ጥበ​ብን ይና​ገ​ራል።

Siga-nos em:



Anúncios