Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


ኢዮብ 40 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መለሰ፥ ኢዮ​ብ​ንም እን​ዲህ አለው፦

2 “በውኑ የሚ​ከ​ራ​ከር ሰው ሁሉን ከሚ​ችል አም​ላክ ጋር ይከ​ራ​ከ​ራ​ልን? ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር የሚ​ዋ​ቀስ እርሱ ይመ​ል​ስ​ለት።”


የኢ​ዮብ መልስ

3 ኢዮ​ብም መለሰ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም እን​ዲህ አለው፦

4 “አንተ ስታ​ስ​ተ​ም​ረኝ እኔ የም​መ​ል​ሰው ምን አለኝ? ይህ​ንስ እየ​ሰ​ማሁ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር እከ​ራ​ከር ዘንድ እኔ ምን​ድን ነኝ? እጄን በአፌ ላይ ከማ​ኖር በቀር የም​መ​ል​ሰው ምን​ድን ነው?

5 አንድ ጊዜ ተና​ገ​ርሁ፥ ሁለ​ተኛ ጊዜም ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ አል​ና​ገ​ርም።”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለኢ​ዮብ እንደ መለ​ሰ​ለት

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ደ​ገና በደ​መና ውስጥ ሆኖ ለኢ​ዮብ መለ​ሰ​ለት፥ እን​ዲ​ህም አለ፦

7 “እን​ግ​ዲህ እንደ ወንድ ወገ​ብ​ህን ታጠቅ፤ እጠ​ይ​ቅ​ሃ​ለሁ፥ አን​ተም መል​ስ​ልኝ።

8 ወይም ፍር​ዴን መቃ​ወ​ም​ህን ተው፥ ጽድ​ቅህ እን​ድ​ት​ገ​ለጥ እንጂ እኔ በሌላ መን​ገድ የም​ፈ​ር​ድ​ብህ ይመ​ስ​ል​ሃ​ልን?

9 እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክንድ ያለ ክንድ አለ​ህን? ወይስ እንደ እርሱ ባለ ድምፅ ታን​ጐ​ደ​ጕ​ዳ​ለ​ህን?

10 እስኪ ልዕ​ል​ና​ንና ኀይ​ልን ተላ​በስ፤ በክ​ብ​ርና በግ​ር​ማም ተጐ​ና​ጸፍ።

11 የቍ​ጣ​ህን መላ​እ​ክት ላክ፤ ትዕ​ቢ​ተ​ኛ​ው​ንም ሁሉ አዋ​ር​ደው።

12 ትዕ​ቢ​ተ​ኛ​ውን ሰው ዝቅ ዝቅ አድ​ር​ገው፤ ዝን​ጉ​ዎ​ች​ንም በአ​ንድ ጊዜ አጥ​ፋ​ቸው።

13 በአ​ፈር ውስጥ በአ​ን​ድ​ነት ሰው​ራ​ቸው፤ ፊታ​ቸ​ው​ንም በኀ​ፍ​ረት ሙላ።

14 በዚ​ያን ጊዜ ቀኝ እጅህ ታድ​ንህ ዘንድ እን​ድ​ት​ችል፥ እኔ ደግሞ እመ​ሰ​ክ​ር​ል​ሃ​ለሁ።

15 “እነሆ፥ በአ​ንተ ዘንድ የዱር አውሬ አለ፤ እንደ በሬ ሣር ይበ​ላል።

16 እነሆ፥ ብር​ታቱ በወ​ገቡ ውስጥ ነው፤ ኀይ​ሉም በሆዱ እን​ብ​ርት ውስጥ ነው።

17 ጅራ​ቱን እንደ ጥድ ዛፍ ያወ​ዛ​ው​ዛል፤ የወ​ር​ቹም ጅማት የተ​ጐ​ነ​ጐነ ነው።

18 የጐ​ድን አጥ​ንቱ እንደ ናስ ነው፤ የጀ​ር​ባው አጥ​ን​ቶ​ችም እንደ ብረት ዘን​ጎች ናቸው።

19 ይህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የፍ​ጥ​ረቱ አውራ ነው። ከተ​ፈ​ጠ​ረም በኋላ መላ​እ​ክት ሣቁ​በት።

20 ወደ ረዥም ተራራ በወጣ ጊዜም በሜ​ዳው ላሉ እን​ስ​ሳት በጥ​ልቁ ስፍራ ደስ​ታን ያደ​ር​ጋል።

21 ጥላ ካለው ዛፍ በታች፥ በደ​ን​ገል፥ በቄ​ጠ​ማና በሸ​ን​በቆ ሥር ይተ​ኛል።

22 ጥላ ያለው ዛፍ በጥ​ላው ይሰ​ው​ረ​ዋል፤ የወ​ንዝ አኻያ ዛፎ​ችም ይከ​ብ​ቡ​ታል።

23 እነሆ፥ ወንዙ ቢጐ​ርፍ አይ​ደ​ነ​ግ​ጥም፤ ዮር​ዳ​ኖ​ስም እስከ አፉ ድረስ ቢፈ​ስስ እርሱ ይተ​ማ​መ​ናል።

24 ዐይኑ እያየ በገ​መድ ይያ​ዛ​ልን? አፍ​ን​ጫ​ውስ ይበ​ሳ​ልን?

25 “በውኑ ዘን​ዶ​ውን በመ​ቃ​ጥን ታወ​ጣ​ለ​ህን? በአ​ፍ​ን​ጫ​ውስ ገመድ ታስ​ራ​ለ​ህን?

26 ወይስ ስናጋ በጕ​ንጩ ታደ​ር​ጋ​ለ​ህን? ወይስ በች​ን​ካር ከን​ፈ​ሩን ትበ​ሳ​ለ​ህን?

27 በውኑ ወደ አንተ እጅግ ይለ​ም​ና​ልን? በጣ​ፈጠ ቃልስ ይና​ገ​ር​ሃ​ልን?

28 በውኑ ከአ​ንተ ጋር ቃል ኪዳን ይገ​ባ​ልን? ወይስ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ባሪያ ይሆን ዘንድ ትወ​ስ​ደ​ዋ​ለ​ህን?

29 ከዎፍ ጋር እን​ደ​ም​ት​ጫ​ወት ከእ​ርሱ ጋር ትጫ​ወ​ታ​ለ​ህን? ወይስ እንደ ልጆች መጫ​ወቻ ዎፍ ታስ​ረ​ዋ​ለ​ህን?

30 አሕ​ዛብ ይመ​ገ​ቡ​ታ​ልን? ወይስ የፊ​ንቄ ሰዎች ይካ​ፈ​ሉ​ታ​ልን?

31 ጀል​ባ​ዎች ሁሉ ቢሰ​በ​ሰቡ የጅ​ራ​ቱን ቍር​በት ሊሸ​ከ​ሙት አይ​ች​ሉም። አጥ​ማ​ጆ​ችም ራሱን በመ​ረብ መያዝ አይ​ች​ሉም።

32 እጅ​ህን በላዩ ጫን፤ በአፉ የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን ጦር​ነት አስብ፥ እን​ግ​ዲ​ህም ወዲህ አት​ድ​ገም፥ አላ​የ​ህ​ምን? ስለ እር​ሱስ የተ​ባ​ለ​ውን አላ​ደ​ነ​ቅ​ህ​ምን?

Siga-nos em:



Anúncios