Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


ኢዮብ 30 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ምዕ​ራፍ 30።

1 “አሁን ግን በዕ​ድሜ ከእኔ የሚ​ያ​ንሱ ለመ​ዘ​ባ​በት በእኔ ላይ ሳቁ፤ አባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን የና​ቅ​ሁ​ባ​ቸ​ውና እንደ መን​ጋዬ ውሾች ያል​ቈ​ጠ​ር​ኋ​ቸው ዛሬ ለብ​ቻ​ቸው ይገ​ሥ​ጹ​ኛል።

2 የእ​ጃ​ቸው ብር​ታት ለእኔ ምን​ድን ነው? ሞት በላ​ያ​ቸው ይምጣ።

3 ትላ​ንት በድ​ካ​ምና በው​ር​ደት ከም​ድረ በዳ ያመ​ለጡ፥ ከረ​ኃብ የተ​ነሣ ተሰ​ድ​ደው ይለ​ም​ናሉ።

4 እየ​ዞሩ የሚ​ለ​ም​ኑና የሚ​በሉ በቅ​ል​ው​ጥም የሚ​ኖሩ ወራ​ዶች፥ ዐመ​ፀ​ኞ​ችና ከበጎ ነገ​ሮች ሁሉ የተ​ቸ​ገሩ ናቸው። ከታ​ላቅ ረኃ​ብም የተ​ነሣ ጨው ጨው የሚ​ለ​ውን የእ​ን​ጨት ሥር ይበ​ላሉ።

5 “ሌቦች በእኔ ላይ ተነሡ፥

6 በሸ​ለ​ቆው ፈረ​ፈ​ርና በም​ድር ጕድ​ጓድ ውስጥ በዓ​ለ​ትም ዋሻ ውስጥ ይኖ​ራሉ፤

7 በገ​ደል ማሚ​ቶው መካ​ከል ይጮ​ኻሉ፤ በሳማ ውስ​ጥም ይሸ​ሸ​ጋሉ።

8 የሰ​ነ​ፎ​ችና የክ​ፉ​ዎች ሰዎች ልጆች ናቸው፤ ስማ​ቸ​ውና ክብ​ራ​ቸው ከም​ድር የጠፋ ነው።

9 አሁ​ንም እኔ መዝ​ፈ​ኛና መተ​ረቻ ሆን​ኋ​ቸው።

10 ተጸ​የ​ፉኝ፥ ከእ​ኔም ራቁ፤ ምራ​ቃ​ቸ​ው​ንም በፊቴ መት​ፋ​ትን አል​ታ​ከ​ቱም።

11 የቀ​ስ​ቱን አፎት ከፍቶ ክፉ አደ​ረ​ገ​ብኝ፤ በፊ​ቴም ልጓ​ሙን ሰደደ።

12 በኀ​ይሉ ቀኝ ተነ​ሣ​ብኝ፤ እግ​ሮ​ቹ​ንም ዘረ​ጋ​ብኝ፤ የሞ​ት​ንም መን​ገድ በእኔ ላይ አደ​ረገ።

13 ፍለ​ጋ​ዬን አጠፋ፤ ልብ​ሴን ገፈ​ፈኝ፥ በቀ​ስ​ቱም ነደ​ፈኝ።

14 እንደ ወደደ አደ​ረ​ገ​ብኝ፤ በመ​ከ​ራም እዛ​ብ​ራ​ለሁ።

15 ድን​ጋጤ በላዬ ተመ​ላ​ለ​ሰ​ች​ብኝ፥ ነፍሴ ከእኔ ላይ እለይ እለይ አለች፥ ደኅ​ን​ነ​ቴም እንደ ተበ​ተነ ደመና አለ​ፈች።

16 “አሁ​ንም ነፍሴ በው​ስጤ ፈሰ​ሰች፤ ጭን​ቀ​ትም በእኔ ላይ ሞላ፤

17 በሌ​ሊት ሁሉ አጥ​ን​ቶች በደዌ ይነ​ድ​ዳሉ፥ ጅማ​ቶ​ችም ይቀ​ል​ጣሉ።

18 ከታ​ላቁ ደዌ ኀይል የተ​ነሣ ልብሴ ተበ​ላ​ሸች፤ የል​ብሴ ክሳድ አነ​ቀ​ችኝ፥ ቀሚ​ሴም በአ​ን​ገቴ ተጣ​በቀ።

19 እርሱ እንደ ጭቃ ረገ​ጠኝ፥ ዕድል ፋን​ታ​ዬም አፈ​ርና አመድ ሆነ።

20 ወደ አንተ ጮኽሁ፥ አል​ሰ​ማ​ኸ​ኝ​ምም፤ እነ​ርሱ ግን ቆመው ተመ​ለ​ከ​ቱኝ።

21 ምሕ​ረት የሌ​ላ​ቸው ሰዎች ደበ​ደ​ቡኝ፥ የገ​ረ​ፈ​ችኝ እጅም በረ​ታች።

22 በኀ​ዘን አኖ​ር​ኸኝ፥ ከሕ​ይ​ወ​ቴም አራ​ቅ​ኸኝ።

23 ሞት እን​ደ​ሚ​ያ​ጠ​ፋኝ አው​ቃ​ለ​ሁና ለሟ​ችም ሁሉ ማደ​ሪ​ያው ምድር ናትና።

24 እኔ ራሴ ልታ​ነቅ በወ​ደ​ድሁ ነበር ይህም ባይ​ሆን ሌላው እን​ዲሁ እን​ዲ​ያ​ደ​ር​ግ​ልኝ እለ​ም​ና​ለሁ።

25 ረዳት ለሌ​ለው ሰው አለ​ቀ​ስሁ የተ​ቸ​ገረ ሰውን ባየሁ ጊዜ ጮኽሁ።

26 ነገር ግን በጎ ነገ​ርን በተ​ጠ​ባ​በ​ቅ​ኋት ጊዜ እነሆ ክፉ ቀኖች መጡ​ብኝ፤ ብር​ሃ​ንን ተስፋ አደ​ረ​ግሁ፥ ጨለ​ማም መጣ​ብኝ።

27 ሆዴ ፈላች፥ አላ​ረ​ፈ​ች​ምም፤ የች​ግ​ርም ዘመን መጣ​ች​ብኝ።

28 በጠ​ባቡ ሄድሁ፥ የሚ​ያ​ሰ​ፋ​ል​ኝም አጣሁ፥ በጉ​ባ​ኤም መካ​ከል ቆሜ እጮ​ኻ​ለሁ።

29 ለሌ​ሊት ዎፍ ወን​ድም፥ ለሰ​ጎ​ንም ባል​ን​ጀራ ሆንሁ።

30 ቍር​በቴ እጅግ ጠቈረ፥ አጥ​ን​ቶቼም ከት​ኩ​ሳት የተ​ነሣ ተቃ​ጠሉ።

31 ስለ​ዚህ ሕማሜ መሰ​ንቆ፥ ልቅ​ሶ​ዬም በገና ሆነ​ብኝ።

Siga-nos em:



Anúncios