Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


ኢዮብ 22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የሦ​ስ​ተ​ኛው ዙር ንግ​ግር

1 ቴማ​ና​ዊ​ውም ኤል​ፋዝ መለሰ፥ እን​ዲ​ህም አለ፦

2 “በውኑ ማስ​ተ​ዋ​ል​ንና ዕው​ቀ​ትን የሚ​ያ​ስ​ተ​ምር፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አይ​ደ​ለ​ምን?

3 አንተ በሥ​ራህ ንጹሕ ከሆ​ንህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምን ያገ​ደ​ዋል? መን​ገ​ድ​ህ​ንስ ብታ​ቀና ምን ይጠ​ቅ​መ​ዋል?

4 አን​ተ​ንስ ተቈ​ጣ​ጥሮ ይዘ​ል​ፍ​ሃ​ልን? ወደ ፍር​ድስ ከአ​ንተ ጋር ይገ​ባ​ልን?

5 “ክፋ​ት​ህስ የበዛ አይ​ደ​ለ​ምን? ኀጢ​አ​ት​ህስ ቍጥር የሌ​ለው አይ​ደ​ለ​ምን?

6 የወ​ን​ድ​ሞ​ች​ህን መያዣ በከ​ንቱ ወስ​ደ​ሃል፥ የታ​ረ​ዘ​ው​ንም ልብ​ሱን ገፍ​ፈ​ሃል።

7 ለተ​ጠማ ውኃ አላ​ጠ​ጣ​ህም፥ የራ​ብ​ተ​ኛ​ው​ንም ጕርሻ ነጥ​ቀ​ሃል፥ ምድ​ርን የሚ​ዘራ ሰውም በው​ስጧ ድን​በ​ርን ያኖ​ራል።

8 ፊታ​ቸ​ውን አይ​ተህ ያደ​ነ​ቅ​ሃ​ቸው አሉ፥ በም​ድ​ርም ላይ ድሆ​ችን በዐ​መፅ ጠላህ

9 መበ​ለ​ቶ​ችን ባዶ​አ​ቸ​ውን ሰድ​ደ​ሃ​ቸ​ዋል፥ ድሃ​አ​ደ​ጎ​ች​ንም አስ​ጨ​ን​ቀ​ሃ​ቸ​ዋል።

10 ስለ​ዚህ አሽ​ክላ ከብ​ቦ​ሃል፥ ከባድ ጦር​ነ​ትም አና​ው​ጦ​ሃል።

11 ብር​ሃ​ኑም ጨለማ ሆነ​ብህ፥ ተኝ​ተ​ህም ሳለህ ውኃው አሰ​ጠ​መህ።

12 “ልዑል የወ​ደ​ደ​ውን ያደ​ርግ ዘንድ የሚ​ገ​ባው አይ​ደ​ለ​ምን? ትዕ​ቢ​ተ​ኞ​ች​ንስ አያ​ዋ​ር​ዳ​ቸ​ው​ምን?

13 አን​ተም እን​ዲህ ብለ​ሃል፦ ኀያል እርሱ ምን ያው​ቃል? በድ​ቅ​ድቅ ጨለማ ውስጥ ሆኖ ሊፈ​ርድ ይች​ላ​ልን?

14 የጠ​ቈረ ደመና ጋር​ዶ​ታል አያ​ይ​ምም፤ በሰ​ማይ ክበብ ላይ ይራ​መ​ዳል።

15 በውኑ ጻድ​ቃን ሰዎች የረ​ገ​ጡ​አ​ትን የዱ​ሮ​ይ​ቱን መን​ገድ ትጠ​ብ​ቃ​ለ​ህን?

16 ጊዜ​ያ​ቸው ሳይ​ደ​ርስ ተነ​ጠቁ፤ መሠ​ረ​ታ​ቸ​ውም እንደ ፈሳሽ ውኃ ፈሰሰ።

17 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምን ያደ​ር​ገ​ናል? ሁሉን የሚ​ችል አም​ላ​ክስ ምን ያመ​ጣ​ብ​ናል? ይላሉ።

18 ነገር ግን ቤታ​ቸ​ውን በመ​ል​ካም ነገር ሞላ፤ የኃ​ጥ​ኣን ምክር ከእ​ርሱ የራ​ቀች ናት።

19 ጻድ​ቃ​ንም አይ​ተው ሳቁ፤ ንጹ​ሓ​ንም በን​ቀት ይዘ​ባ​በ​ቱ​ባ​ቸ​ዋል።

20 በእ​ው​ነት ሀብ​ታ​ቸው ጠፋ፥ የቀ​ረ​ው​ንም እሳት በላች።

21 “አሁ​ንም መታ​ገሥ ትችል እንደ ሆነ፥ ፍሬ​ህም ይበጅ እንደ ሆነ እስኪ ጽኑ ሁን።

22 ከአ​ፉም ሕጉን ተቀ​በል፥ በል​ብ​ህም ቃሉን አኑር፤

23 ብት​መ​ለስ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ራስ​ህን ብታ​ዋ​ርድ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም ከል​ብህ ብታ​ርቅ፥

24 በዓ​ለቱ ቋጥኝ ላይ ለራ​ስህ መዝ​ገ​ብን ታኖ​ራ​ለህ። የሶ​ፎ​ርም ወርቅ እንደ ጅረት ድን​ጋይ ይሆ​ን​ል​ሃል።

25 ሁሉን የሚ​ችል አም​ላ​ክም ከጠ​ላ​ቶ​ችህ ይረ​ዳ​ሃል። ንጽ​ሕ​ና​ንም በእ​ሳት እንደ ተፈ​ተነ ብር አድ​ርጎ ይመ​ል​ስ​ል​ሃል።

26 በዚ​ያን ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ሞገ​ስን ታገ​ኛ​ለህ። ወደ ሰማ​ይም በደ​ስታ ትመ​ለ​ከ​ታ​ለህ።

27 ወደ እር​ሱም ትጸ​ል​ያ​ለህ፥ እር​ሱም ይሰ​ማ​ሃል፤ ስእ​ለ​ት​ህ​ንም ይሰ​ጠ​ሃል።

28 የጽ​ድ​ቅ​ህ​ንም ብድ​ራት ይሰ​ጥ​ሃል። ብር​ሃ​ንም በመ​ን​ገ​ድህ ላይ ይበ​ራል።

29 ራስ​ህን ብታ​ዋ​ርድ ሰውም ኰራ​ብኝ ብትል፥ ራሱን የሚ​ያ​ዋ​ር​ደ​ውን ሰው ያድ​ነ​ዋል።

30 ንጹ​ሕን ሰው ያድ​ነ​ዋል፤ በእ​ጅ​ህም ንጽ​ሕና ትድ​ና​ለህ።”

Siga-nos em:



Anúncios