Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


ኢሳይያስ 38 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የሕ​ዝ​ቅ​ያስ መታ​መ​ምና መዳን

1 በዚ​ያም ወራት ሕዝ​ቅ​ያስ ለሞት እስ​ኪ​ደ​ርስ ታመመ። ነቢ​ዩም የአ​ሞጽ ልጅ ኢሳ​ይ​ያስ ወደ እርሱ መጥቶ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ትሞ​ታ​ለህ እንጂ በሕ​ይ​ወት አት​ኖ​ር​ምና ቤት​ህን አስ​ተ​ካ​ክል” አለው።

2 ሕዝ​ቅ​ያ​ስም ፊቱን ወደ ግድ​ግ​ዳው መልሶ እን​ዲህ ሲል ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸለየ፦

3 “አቤቱ፥ በፊ​ትህ በእ​ው​ነ​ትና በቅን ልብ እንደ ሄድሁ፥ በፊ​ት​ህም ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝ​ህን እን​ዳ​ደ​ረ​ግሁ አስብ።” ሕዝ​ቅ​ያ​ስም እጅግ ታላቅ ልቅ​ሶን አለ​ቀሰ።

4 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ወደ ኢሳ​ይ​ያስ እን​ዲህ ሲል መጣ፤

5 “ሂድ፤ ሕዝ​ቅ​ያ​ስን እን​ዲህ በለው፦ የአ​ባ​ትህ የዳ​ዊት አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ጸሎ​ት​ህን ሰም​ቻ​ለሁ፤ እን​ባ​ህ​ንም አይ​ቻ​ለሁ፤ እነሆ፥ በዕ​ድ​ሜህ ላይ ዐሥራ አም​ስት ዓመት እጨ​ም​ራ​ለሁ፤

6 አን​ተ​ንና ይህ​ች​ንም ከተማ ከአ​ሦር ንጉሥ እጅ አድ​ና​ለሁ፤ ለዚ​ችም ከተማ እቆ​ም​ላ​ታ​ለሁ።

7 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የተ​ና​ገ​ረ​ውን ነገር እን​ዲ​ፈ​ጽ​መው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ምል​ክቱ ይህ ይሆ​ን​ል​ሃል።

8 እነሆ፥ በአ​ባ​ትህ የጥላ ስፍረ ሰዓት ላይ ከፀ​ሐይ ጋራ የወ​ረ​ደ​ውን በደ​ረ​ጃ​ዎች ያለ​ውን ጥላ ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ እን​ዲ​መ​ለስ አደ​ር​ጋ​ለሁ።” ፀሐ​ይም በጥላ ስፍረ ሰዓት ላይ የወ​ረ​ደ​በት ዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ ተመ​ለሰ።


የይ​ሁዳ ንጉሥ የሕ​ዝ​ቅ​ያስ ጸሎት

9 የይ​ሁዳ ንጉሥ ሕዝ​ቅ​ያስ ታምሞ ከደ​ዌው በተ​ፈ​ወሰ ጊዜ የጸ​ለ​የው ጸሎት ይህ ነው፦

10 እኔ እን​ዲህ አልሁ፥ “በሕ​ይ​ወት ዘመኔ መካ​ከል ወደ ሲኦል በሮች እገ​ባ​ለሁ፤ የቀ​ረ​ው​ንም ዘመ​ኔን ተውሁ።

11 ደግ​ሞም፦ በሕ​ያ​ዋን ምድር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ማዳን፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም መዳን በም​ድር ላይ አላ​ይም፤ ከዘ​መ​ዶ​ችም ሰውን አላ​ይም።

12 የቀ​ረ​ው​ንም ኑሬ​ዬን አጣሁ። ከእ​ኔም ወጣች፥ ተለ​የ​ችም። ድን​ኳ​ኑን ተክሎ እን​ደ​ሚ​ያ​ድ​ርና እን​ደ​ሚ​ሄድ፥ ሊቈ​ረጥ እንደ ተቃ​ረበ ሸማም እን​ዲሁ ነፍሴ በላዬ ሆነች።

13 በዚያ ወራት እስ​ኪ​ነጋ ድረስ እንደ አን​በሳ ታወ​ክሁ፤ እን​ደ​ዚ​ሁም አጥ​ን​ቶች ተቀ​ጠ​ቀ​ጡ​ብኝ፤ ከማ​ለዳ ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ተጨ​ነ​ቅሁ።

14 እንደ ሸመላ እን​ዲሁ ጮህሁ፤ እንደ ርግ​ብም አጕ​ረ​መ​ረ​ምሁ፤

15 ዐይ​ኖች ደከሙ፤ ወደ ሰማ​ይም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማየት አል​ቻ​ል​ሁም። ጌታ ሆይ፦ ይቅር በለኝ፤ የሰ​ው​ነ​ቴ​ንም መከራ አር​ቅ​ልኝ።

16 ጌታ ሆይ፥ ስለ እር​ስዋ እን​ዲህ አል​ሁህ፤ ነፍ​ሴን አዳ​ን​ሃት፤ ደስ አለኝ፤ በሕ​ይ​ወ​ትም ኖርሁ።

17 ሰው​ነ​ቴ​ንም እን​ዳ​ት​ጠፋ ይቅር አል​ሃት፤ ኀጢ​አ​ቴ​ንም ሁሉ ወደ ኋላዬ ጣልህ።

18 በመ​ቃ​ብር የሚ​ኖሩ አያ​መ​ሰ​ግ​ኑ​ህ​ምና፤ ሙታ​ንም የሚ​ያ​መ​ሰ​ግ​ኑህ አይ​ደ​ሉ​ምና፤ በሲ​ኦ​ልም የሚ​ኖሩ ይቅ​ር​ታ​ህን ተስፋ አያ​ደ​ር​ጉ​ምና።

19 እኔ ዛሬ እን​ደ​ማ​ደ​ርግ ሕያ​ዋን ብቻ ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ሃል፤ ከዛሬ ጀምሮ ጽድ​ቅ​ህን የሚ​ና​ገሩ ልጆ​ችን እወ​ል​ዳ​ለሁ።

20 ጌታዬ ሆይ አንተ መድ​ኀ​ኒቴ ነህ፤ ስለ​ዚህ በሕ​ይ​ወቴ ዘመን ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አው​ታር ባለው ዕቃ አን​ተን ማመ​ስ​ገ​ንን አላ​ቋ​ር​ጥም።”

21 ኢሳ​ይ​ያ​ስም ሕዝ​ቅ​ያ​ስን እን​ዲህ አለው፥ “የበ​ለስ ጥፍ​ጥፍ አም​ጥ​ተህ በእ​ባጩ ላይ ለብ​ጠው፤ አን​ተም ትፈ​ወ​ሳ​ለህ።”

22 ሕዝ​ቅ​ያ​ስም፥ “ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት እወጣ ዘንድ ምል​ክቱ ምን​ድን ነው?” ብሎ ነበር።

Siga-nos em:



Anúncios