Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


2 ዜና መዋዕል 25 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የይ​ሁዳ ንጉሥ የአ​ሜ​ስ​ያስ ዘመነ መን​ግ​ሥት
( 2ነገ. 14፥2-6 )

1 አሜ​ስ​ያ​ስም መን​ገሥ በጀ​መረ ጊዜ የሃያ አም​ስት ዓመት ጐል​ማሳ ነበረ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ነገሠ፤ እናቱ ኢዮ​ዓ​ዲን የተ​ባ​ለች የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ሴት ነበ​ረች።

2 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ቅን ነገ​ርን አደ​ረገ፤ ነገር ግን በፍ​ጹም ልብ አይ​ደ​ለም።

3 መን​ግ​ሥ​ትም በእጁ በጸ​ና​ለት ጊዜ ንጉ​ሡን አባ​ቱን የገ​ደ​ሉ​ትን ባሪ​ያ​ዎች ገደለ።

4 እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ቃል ኪዳን እንደ ተጻፈ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “ሰው ሁሉ በገዛ ኀጢ​አቱ ይሙት እንጂ አባ​ቶች በል​ጆ​ቻ​ቸው፥ ልጆ​ችም በአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ፋንታ አይ​ሙቱ” ብሎ እን​ዳ​ዘዘ ልጆ​ቻ​ቸ​ውን ግን አል​ገ​ደ​ለም።


በኤ​ዶ​ም​ያስ ላይ የተ​ደ​ረገ ጦር​ነት
( 2ነገ. 14፥7 )

5 ንጉሡ አሜ​ስ​ያ​ስም የይ​ሁ​ዳን ሕዝብ ሰበ​ሰበ፤ እንደ እየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ቤቶች አቆ​ማ​ቸው፤ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ሁሉ የሽህ አለ​ቆ​ች​ንና የመቶ አለ​ቆ​ችን አደ​ረገ፤ ከሃያ ዓመት ጀምሮ ከዚ​ያም በላይ ያሉ​ትን ሁሉ ቈጠረ፤ ለሰ​ል​ፍም የሚ​ወጡ፥ ጋሻና ጦርም የሚ​ይዙ ሦስት መቶ ሺህ የተ​መ​ረጡ ሰዎ​ችን አገኘ።

6 ደግ​ሞም ከእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ መቶ ሺህ ጽኑ​ዓን ኀያ​ላን ሰዎ​ችን በመቶ መክ​ሊት ብር ቀጠረ።

7 አንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው ግን ወደ እርሱ መጥቶ፥ “ንጉሥ ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልና ከኤ​ፍ​ሬም ልጆች ሁሉ ጋር አይ​ደ​ለ​ምና የእ​ስ​ራ​ኤል ጭፍራ ከአ​ንተ ጋር አይ​ውጣ።

8 ብት​ሄድ ግን፥ በእ​ነ​ር​ሱም ማሸ​ነ​ፍን ብታ​ስብ፥ የማ​ጽ​ና​ትና የመ​ጣል ኀይል ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ነውና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጠ​ላ​ቶ​ችህ ፊት ይጥ​ል​ሃል” አለው።

9 አሜ​ስ​ያ​ስም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሰው፥ “ለእ​ስ​ራ​ኤል ጭፍራ የሰ​ጠ​ሁት መቶ መክ​ሊት ምን ይሁን?” አለው። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰው፥ “ከዚህ አብ​ልጦ ይሰ​ጥህ ዘንድ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አይ​ሳ​ነ​ውም” ብሎ መለ​ሰ​ለት።

10 ንጉሡ አሜ​ስ​ያ​ስም ከኤ​ፍ​ሬም ከተ​ሞች የመጡ ጭፍ​ሮች ወደ ስፍ​ራ​ቸው ይመ​ለሱ ዘንድ ለይቶ አሰ​ና​በ​ታ​ቸው፤ ስለ​ዚ​ህም ቍጣ​ቸው በይ​ሁዳ ላይ ጸና፤ ወደ ስፍ​ራ​ቸ​ውም በጽኑ ቍጣ ተመ​ለሱ።

11 አሜ​ስ​ያ​ስም በረታ፤ ሕዝ​ቡ​ንም ሰብ​ስቦ ወደ ጨው ሸለቆ ሄደ፤ ከሴ​ይ​ርም ልጆች ዐሥር ሺህ ገደለ።

12 የይ​ሁ​ዳም ልጆች ደግሞ ዐሥር ሺህ ሰዎ​ችን ማረኩ። ወደ ዐለ​ቱም ራስ ላይ አመ​ጡ​አ​ቸው፤ ከዐ​ለ​ቱም ራስ ላይ ጣሉ​አ​ቸው፤ ሁሉም ተፈ​ጠ​ፈጡ።

13 አሜ​ስ​ያስ ግን ከእ​ርሱ ጋር ወደ ሰልፍ እን​ዳ​ይ​ሄዱ ያሰ​ና​በ​ታ​ቸው ጭፍ​ሮ​ችም ከሰ​ማ​ርያ ጀም​ረው እስከ ቤት​ሮን ድረስ በይ​ሁዳ ከተ​ሞች ላይ አደጋ ጣሉ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ሦስት ሺህ ገደሉ፤ ብዙም ምርኮ ማረኩ።

14 አሜ​ስ​ያ​ስም የኤ​ዶ​ም​ያ​ስን ሰዎች ከገ​ደለ በኋላ የሴ​ይ​ርን ልጆች አማ​ል​ክት አመጣ፤ የእ​ር​ሱም አማ​ል​ክት ይሆኑ ዘንድ አቆ​ማ​ቸው፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም ይሰ​ግ​ድ​ላ​ቸ​ውና ይሠ​ዋ​ላ​ቸው ነበር።

15 ስለ​ዚ​ህም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ በን​ጉሡ በአ​ሜ​ስ​ያስ ላይ መጣ፤ እን​ዲ​ህም ሲል ነቢ​ይን ላከ​በት፥ “ሕዝ​ባ​ቸ​ውን ከአ​ንተ እጅ ያላ​ዳ​ኑ​ትን የአ​ሕ​ዛ​ብን አማ​ል​ክት ስለ​ምን ፈለ​ግ​ሃ​ቸው?”

16 እር​ሱም ይህን ሲና​ገር ንጉሡ አሜ​ስ​ያስ፥ “በውኑ የን​ጉሡ አማ​ካሪ ልት​ሆን ሹሜ​ሃ​ለ​ሁን? ቅጣት እን​ዳ​ያ​ገ​ኝህ ተጠ​ን​ቀቅ” አለው። ነቢ​ዩም፥ “ይህን አድ​ር​ገ​ሃ​ልና፥ ምክ​ሬ​ንም አል​ሰ​ማ​ህ​ምና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሊያ​ጠ​ፋህ እን​ዳ​ሰበ አወ​ቅሁ” ብሎ ዝም አለ።


በይ​ሁ​ዳና በእ​ስ​ር​ኤል መካ​ከል የተ​ደ​ረገ ጦር​ነት
( 2ነገ. 14፥8-20 )

17 የይ​ሁ​ዳም ንጉሥ አሜ​ስ​ያስ ምክር አደ​ረ​ገና፥ “ና፥ እርስ በር​ሳ​ችን ፊት ለፊት እን​ተ​ያይ” ብሎ ወደ እስ​ራ​ኤል ንጉሥ ወደ ኢዩ ልጅ ወደ ኢዮ​አ​ካዝ ልጅ ወደ ኢዮ​አስ ላከ።

18 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ ኢዮ​አስ፦ ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ አሜ​ስ​ያስ እን​ዲህ ሲል ላከ፥ “የሊ​ባ​ኖስ ኵር​ን​ችት ልጅ​ህን ለልጄ ሚስት አድ​ር​ገህ ስጠው” ብሎ ወደ ሊባ​ኖስ ዝግባ ላከ፤ የሊ​ባ​ኖ​ስም ዱር አው​ሬ​ዎች መጥ​ተው ኵር​ን​ች​ቱን ረገ​ጡት።

19 አን​ተም፦ እነሆ፥ ኤዶ​ም​ያ​ስን መት​ቻ​ለሁ ብለህ በል​ብህ ኰር​ተ​ሃል፤ በቤ​ትህ ተቀ​መጥ፤ አንተ ከይ​ሁዳ ጋር ትወ​ድቅ ዘንድ ስለ​ምን መከ​ራን በራ​ስህ ትሻ​ለህ?”

20 የኤ​ዶ​ም​ያ​ስ​ንም አማ​ል​ክት ስለ ፈለጉ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው እጅ አሳ​ልፎ ይሰ​ጣ​ቸው ዘንድ ይህ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ነበ​ረና አሜ​ስ​ያስ አል​ሰ​ማም።

21 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ ኢዮ​አስ ወጣ፤ እር​ሱና የይ​ሁዳ ንጉሥ አሜ​ስ​ያ​ስም በይ​ሁዳ ባለች በቤ​ት​ሳ​ሚስ ላይ እርስ በር​ሳ​ቸው ተያዩ።

22 ይሁ​ዳም በእ​ስ​ራ​ኤል ፊት ድል ሆኑ፥ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ውም ወደ ድን​ኳ​ና​ቸው ሸሹ።

23 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ ኢዮ​አስ የይ​ሁ​ዳን ንጉሥ የአ​ካ​ዝ​ያ​ስን ልጅ የኢ​ዮ​አ​ስን ልጅ አሜ​ስ​ያ​ስን በቤ​ት​ሳ​ሚስ ይዞ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም አመ​ጣው፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ቅጥር ከኤ​ፍ​ሬም በር ጀምሮ እስከ ማዕ​ዘኑ በር ድረስ አራት መቶ ክንድ አፈ​ረሰ።

24 ወር​ቁ​ንና ብሩን ሁሉ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት በአ​ብ​ዲ​ዶም እጅ የነ​በ​ሩ​ትን ዕቃ​ዎች ሁሉ፥ በን​ጉ​ሡም ቤተ መዛ​ግ​ብት የተ​ገ​ኘ​ውን፥ በመ​ያዣ የተ​ያ​ዙ​ት​ንም ልጆች ወስዶ ወደ ሰማ​ርያ ተመ​ለሰ።

25 የይ​ሁዳ ንጉሥ የኢ​ዮ​አስ ልጅ አሜ​ስ​ያስ ከእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ከኢ​ዮ​አ​ካዝ ልጅ ከኢ​ዮ​አስ ሞት በኋላ ዐሥራ አም​ስት ዓመት ኖረ።

26 የቀ​ሩ​ትም የፊ​ተ​ኞ​ቹና የኋ​ለ​ኞቹ የአ​ሜ​ስ​ያስ ነገ​ሮች፥ እነሆ፥ በይ​ሁ​ዳና በእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መጽ​ሐፍ የተ​ጻፈ አይ​ደ​ለ​ምን?

27 አሜ​ስ​ያ​ስም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከመ​ከ​ተል በራቀ ጊዜ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የዐ​መፅ መሐላ አደ​ረ​ጉ​በት፤ ወደ ለኪ​ሶም ኮበ​ለለ፤ በስ​ተ​ኋ​ላ​ውም ወደ ለኪሶ ላኩ፤ በዚ​ያም ገደ​ሉት።

28 በፈ​ረ​ስም ጭነው አመ​ጡት፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ ከአ​ባ​ቶቹ ጋር ቀበ​ሩት።

Siga-nos em:



Anúncios