Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


1 ዜና መዋዕል 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዳዊት በይ​ሁ​ዳና በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ እንደ ነገሠ
( 2ሳሙ. 5፥1-10 )

1 እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ በኬ​ብ​ሮን ወደ ዳዊት ተሰ​ብ​ስ​በው እን​ዲህ አሉት፥ “እነሆ፥ እኛ የአ​ጥ​ን​ትህ ፍላጭ የሥ​ጋህ ቍራጭ ነን፤

2 አስ​ቀ​ድሞ ሳኦል ንጉሥ ሆኖ ሳለ እስ​ራ​ኤ​ልን የም​ታ​ወ​ጣና የም​ታ​ገባ አንተ ነበ​ርህ፤ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፦ ሕዝ​ቤን እስ​ራ​ኤ​ልን አንተ ትጠ​ብ​ቃ​ለህ፤ በሕ​ዝ​ቤም በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ አለቃ ትሆ​ና​ለህ” አለህ።

3 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ሁሉ ወደ ንጉሡ ወደ ኬብ​ሮን መጡ፤ ንጉሥ ዳዊ​ትም በኬ​ብ​ሮን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቃል ኪዳን ከእ​ነ​ርሱ ጋር አደ​ረገ፤ በሳ​ሙ​ኤ​ልም እጅ እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ ዳዊ​ትን ቀቡት።

4 ዳዊ​ትና የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሰዎች ሁሉ ኢያ​ቡስ ወደ​ም​ት​ባል ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሄዱ፤ በሀ​ገ​ሩም የተ​ቀ​መጡ ኢያ​ቡ​ሳ​ው​ያን በዚያ ነበሩ።

5 በኢ​ያ​ቡ​ስም የተ​ቀ​መጡ ዳዊ​ትን፥ “ወደ​ዚህ አት​ገ​ባም” አሉት፤ ዳዊት ግን አን​ባ​ዪ​ቱን ጽዮ​ንን ያዘ፤ እር​ስ​ዋም የዳ​ዊት ከተማ ናት።

6 ዳዊ​ትም ኢያ​ቡ​ሳ​ው​ያ​ንን አስ​ቀ​ድሞ የሚ​መታ ሰው አለ​ቃና መኰ​ንን ይሆ​ናል አለ። የሶ​ር​ህ​ያም ልጅ ኢዮ​አብ አስ​ቀ​ድሞ ወጣና ወጋ​ቸው፥ አለ​ቃም ሆነ።

7 ዳዊ​ትም በአ​ን​ባ​ዪቱ ውስጥ ተቀ​መጠ፤ ስለ​ዚ​ህም “የዳ​ዊት ከተማ” ብለው ጠሩ​አት።

8 ዳዊ​ትም የከ​ተ​ማ​ዋን ዙሪያ ቀጸረ፤ ተዋ​ግ​ቶም እጅ አደ​ረ​ጋት።

9 ዳዊ​ትም ሁሉን ቻይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ርሱ ጋር ነበ​ረና እየ​በ​ረታ ሄደ።


የዳ​ዊት ኀያ​ላን
( 2ሳሙ. 23፥8-39 )

10 ለዳ​ዊ​ትም የነ​በ​ሩት ኀያ​ላን አለ​ቆች እነ​ዚህ ናቸው፤ ስለ እስ​ራ​ኤል እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ያነ​ግ​ሡት ዘንድ ከእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ጋር በመ​ን​ግ​ሥቱ አጸ​ኑት።

11 የዳ​ዊ​ትም ኀያ​ላን ቍጥር ይህ ነበረ፤ የሠ​ላ​ሳው አለቃ የአ​ኪ​ማን ልጅ ኢያ​ቡ​ስቴ ነበረ፤ እርሱ ጦሩን አን​ሥቶ ሦስት መቶ ሰው በአ​ንድ ጊዜ ገደለ።

12 ከእ​ር​ሱም በኋላ በሦ​ስቱ ኀያ​ላን መካ​ከል የነ​በረ የአ​ሆ​ሃ​ዊው የዱዲ ልጅ አል​ዓ​ዛር ነበረ።

13 እርሱ ከዳ​ዊት ጋር በፋ​ሶ​ደ​ሚን ነበረ፥ በዚ​ያም ገብስ በሞ​ላ​በት እርሻ ውስጥ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን ለሰ​ልፍ ተሰ​ብ​ስ​በው ነበር፤ ሕዝ​ቡም ከፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን ፊት ሸሹ።

14 በእ​ር​ሻ​ውም መካ​ከል ቆመው ጠበ​ቁት፥ ያች​ንም ቦታ አዳ​ናት፤ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ን​ንም ገደ​ላ​ቸው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በታ​ላቅ ማዳን አዳ​ና​ቸው።

15 ከሠ​ላ​ሳ​ውም አለ​ቆች ሦስቱ ወር​ደው ዳዊት ወዳ​ለ​በት ወደ ዓለቱ ወደ ዓዶ​ላም ዋሻ መጡ፤ የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም ጭፍራ በኀ​ያ​ላን ሸለቆ ሰፍሮ ነበር።

16 በዚ​ያም ጊዜ ዳዊት በም​ሽጉ ውስጥ ነበረ፤ የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም ጭፍራ በቤተ ልሔም ነበረ።

17 ዳዊ​ትም፥ “በበሩ አጠ​ገብ ካለ​ችው ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ማን ይሰ​ጠ​ኛል?” ብሎ ተመኘ።

18 እነ​ዚህ ሦስቱ ኀያ​ላን የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንን ሰፈር ሰን​ጥ​ቀው ሄዱ፥ በበ​ሩም አጠ​ገብ ካለ​ችው ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ቀዱ፤ ይዘ​ውም ለዳ​ዊት አመ​ጡ​ለት። እርሱ ግን ሊጠጣ አል​ወ​ደ​ደም፥ ነገር ግን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አፍ​ስሶ፦

19 “ይህን አደ​ርግ ዘንድ አም​ላኬ ሆይ፥ ለእኔ አይ​ገ​ባ​ኝም፤ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም ለሞት አሳ​ል​ፈው አም​ጥ​ተ​ው​ታ​ልና የእ​ነ​ዚ​ህን ሰዎች ደም እጠ​ጣ​ለ​ሁን?” አለ። ስለ​ዚ​ህም ዳዊት ይጠ​ጣው ዘንድ አል​ወ​ደ​ደም። ሦስ​ቱም ኀያ​ላን ያደ​ረ​ጉት ይህ ነው።

20 የኢ​ዮ​አ​ብም ወን​ድም አቢሳ የሦ​ስቱ አለቃ ነበረ፤ ሰይ​ፉ​ንም በሦ​ስት መቶ ላይ አን​ሥቶ በአ​ንድ ጊዜ ገደ​ላ​ቸው፤ በሦ​ስ​ቱም መካ​ከል ስሙ የተ​ጠራ ነበረ።

21 በሁ​ለ​ተ​ኛ​ውም ተራ በሆ​ኑት በሦ​ስቱ መካ​ከል የከ​በረ ነበረ፥ አለ​ቃ​ቸ​ውም ሆነ፤ ነገር ግን ወደ ፊተ​ኞቹ ወደ ሦስቱ አል​ደ​ረ​ሰም።

22 በቀ​በ​ሳ​ኤል የነ​በ​ረው፥ ታላቅ ሥራ ያደ​ረ​ገው የጽ​ኑዕ ሰው የዮ​ዳሄ ልጅ በና​ያስ እንደ አን​በሳ ኀያ​ላን የነ​በ​ሩ​ትን ሁለት የሞ​ዓብ ሰዎች ገደለ፤ በአ​መ​ዳ​ይም ወራት ወርዶ በጕ​ድ​ጓድ ውስጥ አን​በሳ ገደለ።

23 ቁመ​ቱም አም​ስት ክንድ የነ​በ​ረ​ውን ረጅ​ሙን ግብ​ፃ​ዊ​ውን ሰው ገደለ፤ በግ​ብ​ፃ​ዊ​ውም እጅ የሸ​ማኔ መጠ​ቅ​ለያ የመ​ሰለ ጦር ነበረ፤ እርሱ ግን በትር ይዞ ወደ እርሱ ወረደ፥ ከግ​ብ​ፃ​ዊ​ውም እጅ ጦሩን ቀምቶ በገዛ ጦሩ ገደ​ለው።

24 የዮ​ዳሄ ልጅ በና​ያስ ያደ​ረ​ገው ይህ ነው፤ ስሙም በሦ​ስቱ ኀያ​ላን መካ​ከል የተ​ጠራ ነበረ።

25 እነሆ፥ ከሠ​ላ​ሳው ይልቅ የከ​በረ ነበረ፤ ነገር ግን ወደ ፊተ​ኞቹ ወደ ሦስቱ አል​ደ​ረ​ሰም። ዳዊ​ትም በና​ያ​ስን በሀ​ገሩ ላይ ሾመው።

26 ደግ​ሞም በጭ​ፍ​ሮቹ ዘንድ የነ​በ​ሩት ኀያ​ላን እነ​ዚህ ናቸው፤ የኢ​ዮ​አብ ወን​ድም አሣ​ሄል፥ የቤተ ልሔሙ ሰው የዱዲ ልጅ ኤል​ያ​ናን፤

27 ሃሮ​ራ​ዊው ሳሞት፥ ፈሎ​ና​ዊው ኬሌስ፤

28 የቴ​ቁሔ ሰው የአ​ቂስ ልጅ ኦራ፥ ዓና​ቶ​ታ​ዊው አቤ​ዔ​ዜር፤

29 ኩሳ​ታ​ዊው ሰቦ​ካይ፥ የአ​ሆ​ሂው ዔላይ፤

30 ነጦ​ፋ​ዊው ሜሐሪ፥ የነ​ጦ​ፋ​ዊው የበ​ዓና ልጅ ሔሌድ፤

31 ከብ​ን​ያም ወገን ከጊ​ብዓ የሪ​ባይ ልጅ ኢታይ፥ ፈር​ኖ​ታ​ዊው ባን​ያስ፤

32 የገ​ዓዝ ወንዝ ሰው ኡሪ፥ ገራ​ባ​ታ​ዊው አብ​ኤል፥

33 ባሮ​ማ​ዊው ዓዝ​ሞት፥ ሰዓ​ል​ቦ​ና​ዊው ኤሊ​ያ​ሕባ፤

34 የጊ​ዞ​ን​ያ​ዊው የኤ​ሳም ልጅ፥ የአ​ሩ​ራ​ዊው የሶላ ልጅ ዮና​ታን፤

35 የአ​ሮ​ራ​ዊው የሳ​ኮር ልጅ አህ​ያም፥ የኤር ልጅ ኤሊ​ፋል፤

36 መከ​ራ​ታ​ዊው ኦፌር፥ ፍሎ​ና​ዊው አኪያ፤

37 ቀር​ሜ​ሎ​ሳ​ዊው ሴራይ፥ የኤ​ዝ​ባይ ልጅ ናራይ፤

38 የና​ታ​ንም ወን​ድም ኢዩ​ኤል፥ የሐ​ገሪ ልጅ ሚብ​ሐር፤

39 አሞ​ና​ዊው ሴሌቅ፥ የሦ​ር​ህያ ልጅ የኢ​ዮ​አብ ጋሻ ጃግሬ ቤሮ​ታ​ዊው ናኮር፤

40 ይት​ራ​ዊው ዔራ፥ ይት​ራ​ዊው ጋሬብ፤

41 ኬጢ​ያ​ዊው ዑር​ያስ፥ የአ​ሕ​ላይ ልጅ ዘባት፤

42 የሮ​ቤ​ላ​ዊው የሲዛ ልጅ ዓዲና፥ እርሱ የሮ​ቤ​ላ​ው​ያን አለቃ ነበረ ከእ​ር​ሱም ጋር ሠላሳ ሰዎች ነበሩ፤

43 የሞካ ልጅ ሐናን፥ ሚት​ና​ዊው ኢዮ​ሣ​ፍጥ፤

44 አስ​ታ​ሮ​ታ​ዊው ዖዝያ፥ የአ​ሮ​ዔ​ራ​ዊው የኮ​ታም ልጆች ሳማና ይዒ​ኤል፤

45 የሳ​ምሪ ልጅ ይዳ​ኤል፥ ወን​ድ​ሙም ቲዳ​ዊው ዮዛሔ፥

46 መዓ​ዊው ኤሊ​ኤል፤ ኢያ​ር​ባኢ፥ ልጁ ዮሳኢ፥ ኤል​ነ​ዓ​ምና ሞዓ​ባ​ዊው ይትማ፤

47 ኤሊ​ኤል፥ ዖቤድ፥ ምሶ​ባ​ዊው ኢያ​ስ​ኤል።

Siga-nos em:



Anúncios