Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


1 ዜና መዋዕል 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ከአ​ዳም እስከ አብ​ር​ሃም ያለው ሐረገ ትው​ልድ
( ዘፍ. 5፥1-32 ፤ 10፥1-32 ፤ 11፥10-26 )

1 አዳም፥ ሴት፥ ሄኖስ፥

2 ቃይ​ናን፥ መላ​ል​ኤል፥ ያሬድ፥

3 ሄኖክ፥ ማቱ​ሳላ፥ ላሜሕ፥

4 ኖኅ፥ ልጆ​ቹም ሴም፥ ካም፥ ያፌት።

5 የያ​ፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዳይ፥ ይሕ​ያን፥ ኤልሳ፥ ቶቤል፥ ሞሳ​ሕና ቲራም።

6 የጋ​ሜ​ርም ልጆች አስ​ካ​ናስ፥ ሪፋት፥ ቶር​ጋማ።

7 የይ​ሕያ ልጆች ኤልሳ፥ ተር​ሴስ፥ ኬቲም፥ ሮድኢ።

8 የካ​ምም ልጆች፤ ኩሽ፥ ምስ​ራ​ይም፥ ፉጥ፥ ከነ​ዓን።

9 የኩ​ሽም ልጆች፤ ሳባ፥ ኤው​ላጥ፥ ሳበታ፥ ሬግ​ማን፥ ሱቦን። የሬ​ግ​ማ​ንም ልጆች፤ ሴባ፥ ዳዳን።

10 ኩሽም ናም​ሩ​ድን ወለደ፤ እር​ሱም በም​ድር ላይ አዳ​ኝና ኀያል መሆ​ንን ጀመረ።

11 ምሥ​ራ​ይም ሎዲ​አ​ምን፥ ዐና​ኒ​ምን፥ ሎቢ​ንን፥ ንፍ​ታ​ሌ​ምን፥

12 ጴጥ​ሮ​ሳ​ኒ​ኤ​ምን፥ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን የወ​ጡ​በ​ትን ከሰ​ሎ​ን​ኤ​ምን፥ ከፋ​ቱ​ሪ​ምን ወለደ።

13 ከነ​ዓን የበ​ኵር ልጁን ሲዶ​ንን፥ ኬጤ​ዎ​ንን፥

14 ኤያ​ቡ​ሴ​ዎ​ንን፥ አሞ​ሬ​ዎ​ንን፥ ጌር​ጌ​ሴ​ዎ​ንን፥

15 አዌ​ዎ​ንን፥ አረ​ቄ​ዎ​ንን፥ ኤሴ​ነ​ዎ​ንን፥

16 አራ​ዴ​ዎ​ንን፥ ሰማ​ሬ​ዎ​ንን፥ አማ​ቲን ወለደ።

17 የሴ​ምም ልጆች፤ አይ​ላም፥ አሡር፥ አር​ፋ​ክ​ስድ፥ ሉድ፥ አራም፥ የአ​ራ​ምም ልጆች፤ ኡስ፥ ዑል፥ ጋቴር፥ ሞሳክ።

18 አር​ፋ​ክ​ስ​ድም ቃይ​ና​ንን ወለደ፤ ቃይ​ና​ንም ሳላን ወለደ፤ ሳላም ኤቦ​ርን ወለደ።

19 ለኤ​ቦ​ርም ሁለት ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ለት፤ በዘ​መኑ ምድር ተከ​ፋ​ፍ​ላ​ለ​ችና የአ​ን​ደ​ኛው ስም ፋሌቅ ተባለ፤ የወ​ን​ድ​ሙም ስም ዮቅ​ጣን ነበረ፤

20 ዮቅ​ጣ​ንም ኤል​ሞ​ዳ​ድን፥ ሣሌ​ፍን፥ ኤራ​ሞ​ትን፥ ያራ​ሕን፥

21 ቄዱ​ራ​ምን፥ ኤዜ​ልን፥ ዲቅ​ላ​ምን፥

22 ጌማ​ሄ​ልን፥ ኤል​ሜ​ሄ​ልን፥ ሳባን፥

23 ኦፌ​ርን፥ ሄው​ላን፥ ኦራ​ምን፥ ዑካ​ብን ወለደ፤ እነ​ዚህ ሁሉ የዮ​ቅ​ጣን ልጆች ነበሩ።

24 የሴ​ምም ልጆች፤ አይ​ላም፥ አሡር፥ አር​ፋ​ክ​ስድ፥ ሳላን፥ ቃይ​ናን፥

25 ዔቦር፥ ፋሌቅ፥ ራግው፥

26 ሴሮሕ፥ ናኮር፥ ታራ፥

27 አብ​ር​ሃም የተ​ባ​ለው አብ​ራም።


የይ​ስ​ማ​ኤል ሐረገ ትው​ልድ
( ዘፍ. 25፥12-16 )

28 የአ​ብ​ር​ሃ​ምም ልጆች፤ ይስ​ሐቅ፥ ይስ​ማ​ኤል።

29 ትው​ል​ዳ​ቸ​ውም እን​ደ​ዚህ ነው። የይ​ስ​ማ​ኤል በኵር ልጅ ናቢ​ዎት፤ ቄዳር፥ ቢዲ​ሄል፥ ሙባ​ሳን፥

30 ሚስ​ማዕ፥ ይዱማ፥ ማሴ፥ ኬዲድ፥ ቴማን፤

31 የጡር፥ ናፌስ፥ ቂዳማ፤ እነ​ዚህ የይ​ስ​ማ​ኤል ልጆች ናቸው።

32 የአ​ብ​ር​ሃም ዕቅ​ብት ኬጡራ የወ​ለ​ደ​ች​ለት ልጆች፤ ዘም​ራን፥ ዮቅ​ሳን፥ ሜዳም፥ ምድ​ያን፥ ዮሳ​ብቅ፥ ስዌሕ፥ የዮ​ቅ​ሳ​ንም ልጆች፤ ሳባ፥ ዳዳን።

33 የም​ድ​ያ​ምም ልጆች፤ ጌፌር፥ ዔፌር፥ ሄኖሕ፥ አቢ​ዳን፥ ኤል​ዳን። እነ​ዚህ ሁሉ የኬ​ጡራ ልጆች ነበሩ።


የኤ​ሳው ሐረገ ትው​ልድ
( ዘፍ. 36፥1-9 )

34 አብ​ር​ሃ​ምም ይስ​ሐ​ቅን ወለደ። የይ​ስ​ሐ​ቅም ልጆች ዔሳ​ውና ያዕ​ቆብ ነበሩ።

35 የዔ​ሳው ልጆች፤ ዔል​ፋዝ፥ ራጉ​ኤል፥ ይዑል፥ ይጉ​ሎም፥ ቆሬ።

36 የኤ​ል​ፋዝ ልጆች፤ ቴማን፥ ኦማር፥ ሳፍር፥ ጎታም፥ ቄኔዝ፥ ቴም​ናስ፥ አማ​ሌቅ።

37 የራ​ጉ​ኤል ልጆች፤ ናቦት፥ ዛራ፥ ሴዴት፥ ሞዛ።

38 የሴ​ይ​ርም ልጆች፤ ሎጣን፥ ሳባን፥ ሴቤ​ጎን፥ ዓናን፥ ዴሶን፥ አሦር፥ ዴሳን።

39 የሎ​ጣ​ንም ልጆች፤ ሖሪ፥ ኤማን፤ ታም​ናን የሎ​ጣን እኅት ነበ​ረች።

40 የሦ​ባል ልጆች፤ ጎለም፥ ማኔ​ሐት፥ ኔባል፥ ሳፍር፥ አናን፤ የሴ​ቤ​ጎን ልጆች፤ ሐያን፥ አናም፤

41 የአ​ናም ልጆች፤ ዴሶን፥ የአ​ናም ሴት ልጅ ኤሌማ፥ የዴ​ሶ​ንም ልጆች፤ አም​ዳን፥ ኤስ​ቦን፥ ኢይ​ት​ራን፥ ካራን፥ እሊህ ናቸው።

42 የአ​ሦር ልጆች፤ በለ​ዓን፥ ዛዕ​ዋን፥ ኢይ​ዓ​ቃን። የዴ​ሶን ልጆች፤ ዖስ፥ አራን።


የኤ​ዶም ነገ​ሥ​ታት
( ዘፍ. 36፥32-43 )

43 በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ላይ ገና ንጉሥ ሳይ​ነ​ግሥ በኤ​ዶ​ም​ያስ ምድር የነ​ገሡ ነገ​ሥ​ታት እነ​ዚህ ናቸው። የቢ​ዖር ልጅ ባላቅ፤ የከ​ተ​ማ​ውም ስም ዲናባ ነበረ።

44 ባላ​ቅም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ የባ​ሶራ ሰው የዛራ ልጅ ኢዮ​ባብ ነገሠ።

45 ኢዮ​ባ​ብም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ የቴ​ማን ሀገር ሰው አሶም ነገሠ፤

46 አሶ​ምም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ በሞ​ዓብ ሜዳ ምድ​ያ​ምን የመ​ታው የባ​ራድ ልጅ አዳድ ነገሠ፤ የከ​ተ​ማ​ውም ስም ጌቴም ነበረ።

47 አዳ​ድም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ የማ​ስቃ ሰው ስማዓ ነገሠ።

48 ስማ​ዓም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ በወ​ንዙ አጠ​ገብ ያለ​ችው የረ​ኆ​ቦት ሰው ሳኦል ነገሠ።

49 ሳኦ​ልም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ የአ​ክ​ቦር ልጅ በኣ​ል​ሐ​ናን ነገሠ።

50 የአ​ክ​ቦር ልጅ በኣ​ል​ሐ​ና​ንም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፋንታ የባ​ራድ ልጅ አዳድ ነገሠ፤ የከ​ተ​ማ​ውም ስም ፌጎር ነበረ፤ ሚስ​ቱም የሚ​ዛ​ሃብ ልጅ የመ​ጥ​ሬድ ልጅ መሄ​ጣ​ብ​ኤል ነበ​ረች።

51 አዳ​ድም ሞተ፤ የኤ​ዶ​ም​ያ​ስም አለ​ቆች እነ​ዚህ ነበሩ፤ ቴም​ናዕ አለቃ፥ ጎለም አለቃ፥ የቴት አለቃ፥

52 አህ​ሊ​ባማ አለቃ፥ ኤላ አለቃ፥ ፌኖን አለቃ፥

53 ቄኔዝ አለቃ፥ ቴማን አለቃ፥ መብ​ሳር አለቃ፥

54 መግ​ዴ​ኤል አለቃ፥ ዛፎ​አል አለቃ፤ እነ​ዚህ የኤ​ዶ​ም​ያስ አለ​ቆች ነበሩ።

Siga-nos em:



Anúncios