Biblia Todo Logo
A Bíblia On-line

- Anúncios -


Este livro não é inspirado por Deus e não faz parte do cânone cristão nem do Tanakh judaico. É apresentado apenas para fins históricos e de estudo. Ver explicação completa

መጽሐፈ ባሮክ 5 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

1 ኢየሩሳሌም ሆይ የኀዘንና የመከራ ልብስሽን አውልቂ፥ ለዘለዓለም ከእግዚአብሔር ክብር የሚወጣውን ውብት ልበሺ።

2 ከእግዚአብሔር የሚመጣውን የጽድቅ ካባ ደርቢ፤ የዘላለማዊውን የክብር አክሊል በራስሽ ላይ ድፊ።

3 እግዚአብሔር የብርሃንሽን ነጸብራቅ ከሰማይ በታች ላሉ ሁሉ ያሳያልና፤

4 ስምሽ ከእግዚአብሔር ዘንድለዘለዓለም “ሰላም፥ ጽድቅና እግዚአብሔርን የመፍራት ክብር” ተብሎ ይጠራል።

5 ኢየሩሳሌም ሆይ ተነሺ! በከፍታ ላይ ቁሚ፤ ወደ ምሥራቅም ተመልከቺ፥ እግዚአብሔር ስላሰባቸው በመደሰት በቅዱሱ ቃል ከምሥራቅና ከምዕራብ የተሰበሰቡትን ልጆችሽን እዪ፤

6 በጠላቶቻቸው ከአንቺ ሲወሰዱ በእግር ነበር፤ እግዚአብሔር ግን እንደ ንጉሥ ዙፋን በክብር ወደ አንቺ ይመልሳቸል።

7 እስራኤል በሰላም በእግዚአብሔር ክብር እንዲሄድ፥ እግዚአብሔር ረጃጅም ተራሮች ሁሉና ኮረብታዎች ዝቅእንዲሉ፥ ሸለቆዎች እንዲሞሉ፥ መሬትም እንዲስተካከል አዟልና።

8 በእግዚአብሔር ትእዛዝ ጫካዎችና መልካም መዓዛ ያለው ዛፍ ሁሉ እስራኤልን በጥላቸው ጋረዱ።

9 እግዚአብሔር እስራኤልን በደስታ፥ በክብሩ ብርሃን፥ ከእርሱ በሚመጣ በምሕረቱና በጽድቁ ይመራቸዋልና።

Siga-nos em:



Anúncios