Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ጥበብ 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሰሎ​ሞን ለጥ​በብ የነ​በ​ረው ፍቅር

1 ጥበብ ከዳ​ርቻ እስከ ዳርቻ ድረስ ደኅና ሆና ትደ​ር​ሳ​ለች፤ በቸ​ር​ነ​ት​ዋም ሁሉን ትሠ​ራ​ለች።

2 እኔም ከጐ​ል​ማ​ሳ​ነቴ ጀምሮ ወደ​ድ​ኋት፤ ፈለ​ግ​ኋ​ትም። ለእ​ኔም ሙሽራ አድ​ርጌ እወ​ስ​ዳት ዘንድ ወደ​ድሁ። ደም ግባ​ት​ዋ​ንም ወደ​ድሁ።

3 የዝ​ም​ድ​ና​ዋም ቸር​ነት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያቀ​ር​ባ​ልና ሁሉን የሚ​ገዛ እርሱ ወደ​ዳት።

4 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምሥ​ጢር ለማ​ወቅ መካር ናትና፥ የሥ​ራ​ውም ወዳጅ ናትና።

5 እር​ሷም ባለ​ች​በት ዘንድ ብል​ጽ​ግና አለ፤ በዚህ ዓለም ገን​ዘብ ላደ​ረ​ጓት ሰዎች ከሁሉ ትመ​ረ​ጣ​ለች፤ ሁሉን የም​ታ​ደ​ርግ ጥበ​ብን የሚ​በ​ል​ጣት ምን​ድን ነው?

6 ዕው​ቀ​ትም ቢደ​ረግ በእ​ርሷ ነው፤ ካሉ​ትም ሁሉ ከእ​ርሷ የሚ​በ​ልጥ ብልህ ማን ነው?

7 እው​ነ​ትን የወ​ደደ ሰውም ቢኖር በእ​ርሷ ነው፤ ድካሟ ያማረ ነውና፥ ንጽ​ሕ​ና​ንና ጥበ​ብን፥ እው​ነ​ት​ንና ብር​ታ​ትን፥ ትሩ​ፋ​ት​ንና ደግ​ነ​ት​ንም ታስ​ተ​ም​ራ​ለች። በዓ​ለሙ ውስ​ጥም በሰው ሕይ​ወት ከእ​ርሷ የሚ​ሻ​ልና የሚ​ጠ​ቅም ምንም የለም።

8 ብዙ ዕው​ቀ​ት​ንና ደግ​ነ​ትን ያወቀ ሰው ቢኖር በእ​ርሷ ነው፤ የቀ​ደ​መ​ው​ንና የሚ​መ​ጣ​ው​ንም ሥራ ያወቀ ሰው ቢኖር በእ​ርሷ ነው፤ የነ​ገር መል​ስ​ንና ፈጥኖ መተ​ር​ጐ​ምን ቢያ​ው​ቅም በእ​ርሷ ነው፤ ተአ​ም​ራ​ት​ንና ድን​ቆ​ችን፥ የጊ​ዜ​ያ​ት​ንና የዓ​መ​ታ​ት​ንም መለ​ዋ​ወጥ አስ​ቀ​ድሞ ቢያ​ውቅ በእ​ር​ስዋ ነው።

9 እኔም፦ ለበጎ ነገር የም​ት​መ​ክ​ርና የም​ት​ገ​ሥጽ ኀዘ​ን​ንና ትካ​ዝን የም​ታ​ስ​ተው እን​ደ​ም​ት​ሆን ዐውቄ ከእኔ ጋራ እን​ድ​ት​ኖር እይ​ዛት ዘንድ ወደ​ድሁ።

10 በእ​ር​ስ​ዋም ምክ​ን​ያት እኔ ጐል​ማ​ሳው በብ​ዙ​ዎች ዘንድ ምስ​ጋ​ናን፥ በሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎ​ችም ዘንድ ክብ​ርን አገ​ኘሁ።

11 ለመ​ፍ​ረድ አሳበ ፈጣን ሆንሁ፤ በኀ​ያ​ላ​ኑም ፊት ተደ​ነ​ቅሁ።

12 ዝም ስልም ታግ​ሠው ይጠ​ብ​ቁኝ ነበር፤ ስና​ገ​ርም ያዳ​ም​ጡኝ ነበር፤ መና​ገ​ርም ባበዛ አፋ​ቸ​ውን በእ​ጃ​ቸው ይይዙ ነበር።

13 በእ​ር​ስ​ዋም ምክ​ን​ያት አለ​መ​ሞ​ትን አገ​ኘሁ፤ ከእ​ኔም በኋላ ለሚ​መጡ ሰዎች ለዘ​ለ​ዓ​ለም መታ​ሰ​ቢ​ያን ተውሁ።

14 ሕዝ​ቡን እሠ​ራራ ነበር፤ አሕ​ዛ​ብም ይገ​ዙ​ልኝ ነበር።

15 የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግጡ የም​ድር መኳ​ን​ን​ትም ሰም​ተው ይፈ​ሩኝ ነበር፤ በሸ​ንጎ ደግ ሆኜ፥ በጠ​ብም ጊዜ ብርቱ ሆኜ እታይ ነበር።

16 ከእ​ርሷ ጋር መኖር መራ​ራ​ነት የለ​በ​ት​ምና፥ ከደ​ስ​ታና ከሐ​ሤ​ትም በቀር ድካ​ምና ኀዘን አይ​ቀ​ር​ብ​ምና ወደ ቤቴ በገ​ባሁ ጊዜ በእ​ርሷ ዐር​ፋ​ለሁ።

17 ይህ​ንም በራሴ ሳስብ ኖርሁ፤ ከኀ​ጢ​አ​ትም መን​ጻት እን​ደ​ማ​ይ​ቻ​ለኝ ዐውቄ በል​ቡ​ናዬ በእ​ር​ስዋ እተ​ጋ​ለሁ፤ የጥ​በብ ዝም​ድ​ናዋ ሕያ​ው​ነት ነውና።

18 በፍ​ቅ​ሯም መል​ካም ደስታ አለ፤ በእ​ጅዋ ሥራም የማ​ያ​ልቅ ብል​ጽ​ግና አለ፤ በነ​ገ​ሯም ውስጥ የዕ​ው​ቀት ትም​ህ​ርት አለ፤ ከእ​ር​ሷም ጋር አንድ በመ​ሆን የሚ​ያ​ስ​መካ ነገር አለ፤ ለራ​ሴም እወ​ስ​ዳት ዘንድ እየ​ፈ​ለ​ግ​ኋት ሀገ​ሩን ዞርሁ።

19 እኔ ዐዋቂ ልጅ ነኝ፤ ሰው​ነ​ቴም በጎ ሆነ​ች​ልኝ።

20 ደግ ነኝና ወደ ንጹሕ ሥጋዋ ገባሁ።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እር​ሷን ካል​ሰ​ጠኝ በቀር እን​ደ​ማ​ላ​ገ​ኛት በዐ​ወ​ቅሁ ጊዜ ይህ ምክር ከጥ​በብ ሆነ፤ የማን ስጦ​ታም እንደ ሆነች ዐውቅ ዘንድ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸለ​ይሁ፥ ለመ​ን​ሁ​ትም።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos