Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ጥበብ 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የጣ​ዖት አም​ልኮ ከን​ቱ​ነት

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የማ​ወቅ ጕድ​ለት በል​ቡ​ና​ቸው ያለ​ባ​ቸው ሰዎች ሁሉ በእ​ው​ነት ከንቱ ናቸ​ውና፥ በሚ​ታዩ መል​ካም ነገ​ሮች ያለ​ውን ያውቁ ዘንድ ተሳ​ና​ቸው፥ ሥራ​ው​ንም እያዩ ሠሪ​ውን አላ​ወ​ቁ​ትም።

2 ነገር ግን እሳ​ት​ንና ፈጥኖ የሚ​ነ​ፍ​ሰ​ውን ነፋስ፥ ወይም የከ​ዋ​ክ​ብ​ትን ዙረት፥ ወይም የው​ኃ​ውን ሞገድ፥ ወይም የሰ​ማይ ብር​ሃ​ና​ትን ዓለ​ሙን የሚ​ያ​ስ​ተ​ዳ​ድሩ አማ​ል​ክት አስ​መ​ሰ​ሏ​ቸው።

3 በመ​ል​ካ​ቸው ውበት ደስ ባላ​ቸው ጊዜ እነ​ዚ​ህን ፍጥ​ረ​ታት አማ​ል​ክት ካደ​ረ​ጓ​ቸው፥ ውበ​ትን የፈ​ጠረ እርሱ ይህን ፍጥ​ረት ፈጥ​ሯ​ልና የእ​ነ​ዚህ ጌታ ፈጽሞ እን​ደ​ሚ​በ​ልጥ ይወቁ።

4 ከኀ​ይ​ላ​ቸ​ውና ከሥ​ራ​ቸው የተ​ነሣ ከተ​ደ​ነ​ቁስ የፈ​ጠ​ራ​ቸው እርሱ ፈጽሞ ኀያል እንደ ሆነ ያስ​ተ​ውሉ።

5 ፍጡ​ራን የፍ​ጥ​ረ​ታ​ትን ውበት ታላ​ቅ​ነት አይ​ተው የፍ​ጥ​ረ​ታ​ትን ፈጣሪ በእ​ርሱ መስ​ለ​ው​ታል።

6 ነገር ግን ከዚህ ጋራ ዳግ​መኛ አም​ላ​ክን እየ​ፈ​ለ​ጉት፥ ያገ​ኙ​ትም ዘንድ እየ​ወ​ደዱ ቢሳ​ሳቱ፥ በእ​ነ​ርሱ ላይ የሚ​ኖ​ረው ነቀፋ ጥቂት አይ​ደ​ለም።

7 ወደ ሥራው ተመ​ል​ሰው በፈ​ለ​ጉት ነበ​ርና፥ እነ​ርሱ ግን በማ​የት አበቁ፥ የሚ​ታ​ዩት መል​ካ​ሞች ናቸ​ውና።

8 ዳግ​መ​ኛም ምክ​ን​ያ​ታ​ቸው ብዙ ነው።

9 ዓለ​ምን መረ​ዳት እስ​ኪ​ገ​ባ​ቸው ድረስ ይመ​ለ​ከቱ ዘንድ ይህን ያህል ከተ​ቻ​ላ​ቸው የእ​ነ​ዚ​ህን ጌታ ፈጥ​ነው ያገ​ኙት ዘንድ እን​ዴት አል​ቻ​ሉም?

10 ከወ​ር​ቅና ከብር በጥ​በብ የተ​ሠሩ የሰው እጅ ሥራ​ዎ​ችን፥ የእ​ን​ስሳ ምሳ​ሌን፥ ወይም የማ​ይ​ጠ​ቅም የጥ​ንት የእጅ ሥራ ድን​ጋ​ይን አማ​ል​ክት ብለው የሚ​ጠሩ እነ​ዚህ ጐስ​ቋ​ሎች ናቸው፥ ተስ​ፋ​ቸ​ውም በሞቱ ነገ​ሮች ላይ ነው።

11 የሚ​ታ​የ​ው​ንና የሚ​ወ​ዛ​ወ​ዘ​ውን እን​ጨት የሚ​ጠ​ርብ ጠራቢ ቢኖር መል​ካም ሆኖ የበ​ቀ​ለ​ውን እን​ጨት ይቈ​ር​ጣል፥ ቅር​ፊ​ቱን ሁሉ በጥ​በብ ይጠ​ር​ባል፤ መል​ካም አድ​ር​ጎም ይሠ​ራ​ዋል፥ ለኑሮ አገ​ል​ግ​ሎ​ትም የሚ​ጠ​ቅም ዕቃ አድ​ርጎ ይሠ​ራ​ዋል።

12 ምግ​ቡ​ንም ለማ​ዘ​ጋ​ጀት የሥ​ራ​ውን ጠረባ ከፈ​ጸመ በኋላ ይጠ​ግ​ባል።

13 ዳግ​መ​ኛም ለም​ንም ከማ​ይ​ጠ​ቅም እን​ጨት የተ​ረፈ ጕማ​ጁን፥ ጕጣ​ሙ​ንና ጫፉ ሁሉ የጠ​መ​መ​ውን እን​ጨት ወስዶ ሥራ​ውን በማ​ስ​ተ​ን​ተን ይጠ​ር​በ​ዋል፥ ከዚ​ህም በኋላ በቦ​ዘ​ነ​በት ቀን በሰው መልክ መስሎ ይቀ​ር​ፀ​ዋል።

14 ወይም ከንቱ በሚ​ሆን በእ​ን​ስሳ ምስል ይሠ​ራ​ዋል፥ በቀይ ቀለ​ምም ይቀ​ባ​ዋል፤ በጣ​ቱም ቀለም አግ​ብቶ ቀይ ያደ​ር​ገ​ዋል። ያለ​በ​ት​ንም ጕድ​ለት ይሞ​ላል።

15 ለእ​ር​ሱም የሚ​ገባ የው​ቅር ቤት ይሠ​ራል፤ በሠ​ራ​ለት ቦታም ያኖ​ረ​ዋል፥ ከግ​ድ​ግ​ዳ​ውም አስ​ጠ​ግቶ በብ​ረት ይቸ​ነ​ክ​ረ​ዋል።

16 ምስል ነውና፥ የሚ​ረ​ዳ​ው​ንም ይፈ​ል​ጋ​ልና ራሱን መር​ዳት እን​ደ​ማ​ይ​ችል ዐውቆ እን​ዳ​ይ​ወ​ድ​ቅ​በት ይጠ​ነ​ቀ​ቃል።

17 ከዚ​ህም በኋላ ስለ ገን​ዘ​ቡና ስለ ሚስቱ፥ ስለ ልጆ​ቹም ወደ እርሱ ይለ​ም​ናል፤ ነፍስ ከሌ​ለው ከጣ​ዖቱ ጋርም ሲነ​ጋ​ገር አያ​ፍ​ርም።

18 ስለ ፈውስ ወደ በሽ​ተ​ኛው ይለ​ም​ናል፥ ስለ ሕይ​ወ​ትም መዋ​ቲ​ውን ይለ​ም​ናል፥ ስለ ርዳ​ታም መር​ዳት ወደ​ማ​ይ​ች​ለው ደካማ ይማ​ል​ዳል።

19 ስለ መን​ገ​ድም ነገር ይን​ቀ​ሳ​ቀስ ዘንድ ወደ​ማ​ይ​ቻ​ለ​ውና አን​ዲት ርም​ጃን ወደ​ማ​ይ​ራ​መ​ደው ይለ​ም​ናል። ስለ ብል​ጽ​ግ​ናና ስለ ሥራም፥ ስለ ማግ​ኘ​ትም፥ የእ​ጅን ሥራም ስለ ማቅ​ናት እጆቹ ምንም ወደ​ማ​ይ​ሠሩ ይለ​ም​ናል፥ ኀይ​ል​ንና ሥራ ማፍ​ጠ​ን​ንም ይሰ​ጠው ዘንድ ምንም ኀይል ከሌ​ለው ከእ​ርሱ ይፈ​ል​ጋል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos