Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ጥበብ 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ጥበብ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ሕዝብ በበ​ርሃ እንደ መራ​ቻ​ቸው

1 እር​ስዋ በቅ​ዱሱ ነቢይ እጅ ሥራ​ቸ​ውን አቃ​ናች፤

2 ማንም ወዳ​ል​ኖ​ረ​በት ምድረ በዳም ሄደው ኖሩ። ባል​ተ​ረ​ገ​ጠች ቦታም የድ​ን​ኳ​ኖ​ቻ​ቸ​ውን ካስማ ተከሉ።

3 ተዋ​ጊ​ዎ​ች​ንም ተቋ​ቋ​ሟ​ቸው፤ ጠላ​ቶ​ች​ንም ተበ​ቀ​ሏ​ቸው።

4 በተ​ጠሙ ጊዜም ጠሩህ፥ ከዐ​ለት ድን​ጋ​ይም ውኃ ተሰ​ጣ​ቸው። ከጽኑ ድን​ጋ​ይም ለጥ​ማ​ቸው ፈውስ ተሰ​ጣ​ቸው።

5 ጠላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም በዚህ ሥራ ተፈ​ር​ዶ​ባ​ቸው ጠፉ።

6 በዚ​ህም ተቸ​ግ​ረው በተ​ጨ​ነቁ ጊዜ በጎ ነገ​ርን አደ​ረ​ግ​ህ​ላ​ቸው።

7 በተ​ገ​ደ​ሉት ሰዎች ደም እነ​ዚያ ባደ​ፈ​ረ​ሱት በማ​ይ​ጐ​ድ​ለው ወንዝ ምንጭ ፋንታ፥

8 ሕፃ​ናት በዐ​ዋጅ መገ​ደ​ላ​ቸ​ውን ለመ​ዝ​ለፍ በተ​ስፋ ሳታ​ስ​ጠ​ብቅ ፈጥ​ነህ ያመ​ነ​ጨ​ኸ​ውን ብዙ ውኃ ሰጠ​ኻ​ቸው።

9 እን​ደ​ዚ​ሁም በተ​ጠሙ ጊዜ ስለ​ተ​ፈ​ታ​ተ​ኑህ ተቃ​ዋ​ሚ​ዎ​ችን ፈረ​ድ​ህ​ባ​ቸው።

10 እነ​ርሱ ግን በም​ሕ​ረ​ትህ ተገ​ሠጹ፥ ክፉ​ዎ​ችም በመ​ዓት በተ​ፈ​ረ​ደ​ባ​ቸው ጊዜ እን​ዴት እንደ ተቀጡ ዐወቁ።

11 እነ​ዚ​ህ​ንም እን​ደ​ሚ​ቀጣ አባት ገሠ​ጽ​ኻ​ቸው። እነ​ዚ​ያን ግን ርኅ​ራኄ እን​ደ​ሌ​ለው ንጉሥ ተከ​ት​ለህ ቀጣ​ኻ​ቸው።

12 በዚ​ህም አም​ሳል ገረ​ፍ​ኻ​ቸው። ሳሉም፥ ሳይ​ኖ​ሩም አሳ​ዘ​ን​ኻ​ቸው።

13 እጥፍ ኀዘን አግ​ኝ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ ያለ​ፈ​ው​ንም ክፉ ነገር የማ​ሰብ ጩኸት አግ​ኝ​ት​ዋ​ቸ​ዋ​ልና።

14 በመ​ከ​ራ​ቸ​ውም በጎ ነገር እን​ዳ​ደ​ረ​ገ​ላ​ቸው በሰሙ ጊዜ እነ​ርሱ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ገኘ ደስታ አደ​ረ​ጉት።


በኃ​ጥ​ኣን ላይ የሚ​ደ​ርስ ቅጣት

15 ዳግ​መ​ኛም በክ​ፋት ቀድሞ የጣ​ሉ​ትን አጡት፤ ከዚ​ህም በኋላ በመ​ዘ​ባ​በት ከእ​ርሱ ሸሹ፤ ከት​እ​ዛዙ መው​ጣት ፍጻሜ የተ​ነ​ሣም አደ​ነቁ፥ ጻድ​ቃ​ንም እንደ ተጠሙ እነ​ርሱ የተ​ጠሙ አይ​ደ​ሉም።

16 አእ​ምሮ በሌ​ላት በል​ቡ​ና​ቸው ክፋት በሳ​ቱ​ባት ጊዜ፥ የማ​ይ​ና​ገር፥ የተ​ና​ቀና ከንቱ ሀብት እን​ስ​ሳን አም​ል​ከ​ዋ​ልና፥

17 ሰው በበ​ደ​ለ​በት ሥራ እን​ዲ​ፈ​ረ​ድ​በት ያውቁ ዘንድ ለመ​በ​ቀል የማ​ይ​ና​ገር ብዙ እን​ስ​ሳን ላክ​ህ​ባ​ቸው።

18 ዓለ​ምን ካለ​መ​ኖር ለፈ​ጠረ ሁሉን ለሚ​ችል ቀኝ እጅህ ብዙ ድቦ​ች​ንና ቍጡ አን​በ​ሶ​ችን ትል​ክ​ባ​ቸው ዘንድ አይ​ሳ​ነ​ው​ምና።

19 ያም ባይ​ሆን ድን​ገት የተ​ፈ​ጠሩ የማ​ይ​ታ​ወቁ፥ የሚ​ያ​ላ​ል​ብና የሚ​ፋጅ እሳ​ትን የሚ​ተ​ነ​ፍሱ፥ ያም ባይ​ሆን የሚ​ከ​ረፋ የጢስ መዓ​ዛን የሚ​ተ​ነ​ፍሱ፥ ያም ባይ​ሆን ከክፉ ዓይ​ና​ቸው የእ​ሳት ፍን​ጣ​ሪን ቦግ ቦግ የሚ​ያ​ደ​ርጉ ቍጣን የተ​ሞሉ አው​ሬ​ዎ​ችን ላክ​ህ​ባ​ቸው።

20 ሊያ​ጠ​ፋ​ቸው የሚ​ችል ክፋ​ታ​ቸው ወይም ፍር​ዳ​ቸው ብቻ አይ​ደ​ለም። ነገር ግን መል​ካ​ቸው ባስ​ፈ​ራ​ቸ​ውና ባጠ​ፋ​ቸው ነበር።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀያል መሓ​ሪም ስለ መሆኑ

21 ከዚ​ህም በቀር፦ ስታ​ባ​ር​ራ​ቸው፥ በኀ​ይ​ልህ መን​ፈ​ስም ስታ​ጠ​ፋ​ቸው፥ በአ​ን​ዲት ምል​ክት ይጠፉ ዘንድ በተ​ገ​ባ​ቸው ነበር። ነገር ግን ሁሉን በመ​ጠን፥ በቍ​ጥ​ርና በሚ​ዛን ሠራህ።

22 የከ​ሃ​ሊ​ነ​ትህ ገና​ና​ነት በአ​ንተ ዘንድ ሁል​ጊዜ ይኖ​ራ​ልና፥ የክ​ን​ድህ ጽን​ዐት ኀይ​ል​ንም ማን ይቃ​ወ​ማ​ታል?

23 ዓለሙ ሁሉ በፊ​ትህ እንደ ሚዛን ውል​ብ​ል​ቢት ነውና፥ በማ​ለ​ዳም በም​ድር ላይ እንደ ወረ​ደች እንደ ጠል ጠብታ ነውና።

24 አንተ ሁሉን የም​ት​ችል ነህና ሁሉን ይቅር ትላ​ለህ፥ ለን​ስ​ሓም እየ​ጠ​በ​ቅ​ኸው የሰ​ውን ኀጢ​አት ቸል ትላ​ለህ።

25 ያሉ​ትን ሁሉ ትወ​ዳ​ለህ፥ ከፈ​ጠ​ር​ኸው ፍጥ​ረ​ትም ምንም የም​ት​ን​ቀው የለም፥ ብት​ጠ​ላ​ውስ ኖሮ አት​ፈ​ጥ​ረ​ውም ነበ​ርና።

26 አንተ ካል​ወ​ደ​ድ​ኸው በፊ​ትህ እን​ደ​ምን በጸና ነበር! አን​ተስ ካል​ጠ​ራ​ኸው እን​ደ​ምን በተ​ጠ​በቀ ነበር!

27 ለፍ​ጥ​ረ​ቱም ሁሉ ትራ​ራ​ለህ፥ ይቅ​ርም ትላ​ለህ። ሰውን የም​ት​ወ​ድድ አቤቱ፥ ሁሉ ያንተ ነውና፥

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos