Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ጥበብ 10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ጥበብ ሰውን እን​ደ​ም​ት​ጠ​ብቅ

1 ይህቺ አስ​ቀ​ድሞ የተ​ፈ​ጠረ የዓ​ለ​ምን አባት ጠበ​ቀች፥ ብቻ​ው​ንም ከተ​ፈ​ጠረ በኋላ እንደ አደራ ጠበ​ቀ​ችው፥ ከራሱ በደ​ልም አዳ​ነ​ችው።

2 ሁሉ​ንም ይገ​ዛና ይይዝ ዘንድ ኀይ​ልን ሰጠ​ችው ።

3 በደ​ለ​ኛና ግፈኛ ሰውም በቍ​ጣው ከእ​ርሷ በራቀ ጊዜ፥ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውን ከሚ​ገ​ድሉ ሰዎች ጋር በመ​ዓት ጠፋ።

4 ዳግ​መ​ኛም ምድር በማየ አይኅ በጠ​ፋች ጊዜ ጥበብ ጻድ​ቁን አዳ​ነ​ችው፥ በተ​ናቀ እን​ጨት ዕቃም አሻ​ገ​ረ​ችው።

5 አሕ​ዛብ ወደ ተለ​ያየ ክፋ​ትና ጥመት ተጨ​ል​ጠው በሄዱ ጊዜ ጻድ​ቁን አመ​ለ​ከ​ተ​ችው፤ ያለ በደ​ልና ያለ ነውር ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጠበ​ቀ​ችው፤ በቸ​ር​ነ​ትም የጸና ልጁን ጠበ​ቀች።

6 ይህቺ ከሚ​ጠፉ ዝን​ጉ​ዎች ሰዎች ለይታ ጻድ​ቁን ልጅ አዳ​ነች፥ በአ​ም​ስቱ ከተ​ሞ​ችም ላይ እሳት በወ​ረ​ደች ጊዜ በመ​ሸሽ አዳ​ነ​ችው።

7 ለክ​ፋ​ታ​ቸው ምስ​ክር ልት​ሆን እስከ ዛሬ ድረስ ምድረ በዳ ሆና እየ​ጤ​ሰች አለች፥ ተክ​ሎ​ች​ዋም በጊ​ዜዋ ቢያ​ፈሩ ፍጹ​ማን ያል​ሆኑ ናቸው፤ ያላ​መ​ነች ሰው​ነ​ትም መታ​ሰ​ቢያ ሆኖ የሚ​ታይ የጨው ድን​ጋይ ሆና ቆማ​ለች።

8 እነ​ዚህ ጥበ​ብን የተ​ላ​ለፉ ናቸ​ውና ደግ ነገ​ርን ባለ​ማ​ወቅ የደ​ረ​ሰ​ባ​ቸ​ውን መዓት በማ​ወቅ እንደ እነ​ዚያ የጠፉ ብቻ አይ​ደ​ለም። ነገር ግን የበ​ደ​ሉ​ትን በደል መሰ​ወር እን​ዳ​ል​ተ​ቻ​ላ​ቸው መጠን ለስ​ን​ፍ​ና​ቸው መታ​ሰ​ቢ​ያን በዚህ ዓለም ተዉ።

9 ጥበ​ብስ የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሏ​ትን ሰዎች ከድ​ካ​ምና ከመ​ከራ አዳ​ነች።

10 ይህች ከወ​ን​ድሙ ቍጣ የተ​ነሣ የሸ​ሸ​ውን ጻድቅ ሰው ወደ ቀና መን​ገድ መራ​ችው። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም መን​ግ​ሥት አሳ​የ​ችው፤ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ት​ንም ማወ​ቅን ሰጠ​ችው፥ ከድ​ካሙ የተ​ነ​ሣም አበ​ለ​ጸ​ገ​ችው፥ ጥሪ​ቱ​ንም አበ​ዛ​ች​ለት።

11 ከሚ​ቀ​ሙ​ትና ከሚ​በ​ረ​ታ​ቱ​በ​ትም ሰዎች የተ​ነሣ ጠበቃ ሆና ቆመ​ች​ለት፤ ረዳ​ች​ውም።

12 ከጠ​ላ​ቶ​ቹም እንደ አደራ ዕቃ ጠበ​ቀ​ችው፥ ከከ​በ​ቡ​ትም ሰዎች አዳ​ነ​ችው። ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በበጎ መገ​ዛት ከሁሉ እን​ደ​ሚ​ጸና ያውቅ ዘንድ በጽኑ ገድል ጊዜ ድልን ሰጠ​ችው።

13 ይሀቺ ጥበብ በተ​ሸጠ ጊዜ ጻድ​ቁን ሰው አል​ተ​ለ​የ​ች​ውም፤ ነገር ግን ወደ ጕድ​ጓድ ከእ​ርሱ ጋር ወረ​ደች፥ ከኀ​ጢ​አ​ትም አዳ​ነ​ችው።

14 በተ​በ​ረ​ታ​ቱ​በ​ትም ሰዎች ላይ ግዛ​ት​ንና የመ​ን​ግ​ሥ​ትን ሹመት እስ​ከ​ም​ታ​መ​ጣ​ለት ድረስ በታ​ሠ​ረ​በት አል​ተ​ለ​የ​ች​ውም። የና​ቁ​ት​ንና ያነ​ወ​ሩ​ት​ንም ሐሰ​ታ​ቸ​ውን ገለ​ጠ​ች​ባ​ቸው። የዘ​ለ​ዓ​ለ​ም​ንም ክብር ሰጠ​ችው።


ጥበብ እስ​ራ​ኤ​ልን ከግ​ብፅ መርታ እን​ዳ​ወ​ጣ​ቻ​ቸው

15 ይህ​ቺም ጥበብ ጻድቅ ሕዝ​ብን፥ ነቀፋ የሌ​ለ​በት ዘር​ንም ከሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቋ​ቸው አሕ​ዛብ አዳ​ነች።

16 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪያ ሰው​ነ​ትም አደ​ረች፤ በተ​አ​ም​ራ​ትና በድ​ንቅ ሥራ​ዎ​ችም የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግጡ ነገ​ሥ​ታ​ትን ተቃ​ወ​መች።

17 ለቅ​ዱ​ሳ​ንም የድ​ካ​ማ​ቸ​ውን ዋጋ ሰጠ​ቻ​ቸው፥ የተ​ደ​ነቀ መን​ገ​ድ​ንም መራ​ቻ​ቸው፥ በቀ​ንም ጥላ ሆነ​ቻ​ቸው፥ በሌ​ሊ​ትም ስለ ከዋ​ክ​ብት ብር​ሃን ፈንታ ብር​ሃን ሆና አበ​ራ​ች​ላ​ቸው።

18 የሚ​ያ​ስ​ፈራ የኤ​ር​ትራ ባሕ​ር​ንም አሻ​ገ​ረ​ቻ​ቸው፥ በብዙ ውኃ መካ​ከ​ልም አሳ​ለ​ፈ​ቻ​ቸው።

19 ጠላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ግን አሰ​ጠ​መች፥ እነ​ር​ሱ​ንም ከጥ​ልቅ ባሕር አወ​ጣ​ቻ​ቸው።

20 ስለ​ዚ​ህም ነገር ጻድ​ቃን ክፉ​ዎ​ችን ማረኩ። አቤቱ ቅዱስ ስም​ህ​ንም አመ​ሰ​ገኑ። ተዋ​ጊና አሸ​ናፊ እጅ​ህ​ንም በአ​ን​ድ​ነት አከ​በሩ።

21 ጥበብ የዲ​ዳ​ዎ​ችን አፍ ከፍ​ታ​ለ​ችና፥ የሕ​ፃ​ና​ት​ንም አን​ደ​በት ቀንቶ የሚ​ና​ገር አድ​ር​ጋ​ለ​ችና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos