Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ሲራክ 48 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ነቢዩ ኤል​ያስ

1 ነቢዩ ኤል​ያ​ስም እንደ እሳት ተነሣ፥ ቃሉም እንደ ነበ​ል​ባል ያቃ​ጥል ነበር።

2 ረኃ​ብ​ንም አመ​ጣ​ባ​ቸው፤ በቅ​ን​ዓ​ቱም አሳ​ነ​ሳ​ቸው።

3 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ሰማ​ይን ዘጋው፤ ከሰ​ማ​ይም እሳ​ትን ሦስት ጊዜ አወ​ረደ።

4 ኤል​ያስ ሆይ፥ በተ​አ​ም​ራ​ትህ እን​ዴት ከበ​ርህ! እን​ዳ​ን​ተስ የተ​መካ ማን​ነው?

5 በል​ዑል ቃል ከሞቱ ሰዎች ለይቶ ምው​ትን ከመ​ቃ​ብር ያስ​ነሣ ማን​ነው?

6 ነገ​ሥ​ታ​ቱን ወደ ሞት፥ የከ​በሩ ሰዎ​ቹ​ንም ከአ​ል​ጋ​ቸው ያወ​ረ​ዳ​ቸው ማን​ነው?

7 በሲና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ተግ​ሣጽ፥ በኮ​ሬ​ብም የበ​ቀ​ልን ፍርድ የሰማ ማን​ነው?

8 ይበ​ቀሉ ዘንድ ነገ​ሥ​ታ​ቱን፥ ከእ​ር​ሱም ቀጥሎ ይተኩ ዘንድ ነቢ​ያ​ትን የቀ​ባ​ቸው ማን​ነው?

9 በእ​ሳት ሠረ​ገ​ላና በእ​ሳት ፈረስ ወደ ሰማይ የወጣ ማን​ነው?

10 መቅ​ሠ​ፍቱ ከመ​ው​ረዱ አስ​ቀ​ድሞ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቍጣ ይመ​ልስ ዘንድ፥ የአ​ባ​ት​ንም ልብ ወደ ልጅ ይመ​ልስ ዘንድ፤ የያ​ዕ​ቆ​ብ​ንም ወገ​ኖች ያጸ​ና​ቸው ዘንድ በተ​ወ​ሰነ ዘመን የተ​ጻ​ፈ​ለት ማን​ነው?

11 የሚ​ያ​ው​ቁ​ህና በፍ​ቅ​ርህ ያጌጡ ሰዎች ብፁ​ዓን ናቸው፥ እኛም ስለ አንተ በሕ​ይ​ወት እን​ኖ​ራ​ለን።


ነቢዩ ኤል​ሳዕ

12 በእ​ሳት ሠረ​ገላ ወደ ላይ የወጣ ኤል​ያስ ነው፤ ከእ​ር​ሱም መን​ፈስ የተ​መላ ኤል​ሳዕ ነበረ፤ በዘ​መ​ኑም አለ​ቆች አላ​ስ​ደ​ነ​ገ​ጡ​ትም፤ ማንም እር​ሱን የተ​ቋ​ቋ​መው አል​ነ​በ​ረም።

13 ከነ​ገ​ሩም ሁሉ የተ​ሳ​ነው አል​ነ​በ​ረም፤ ከሞ​ተም በኋላ በድኑ ትን​ቢ​ትን ተና​ገረ።

14 በሕ​ይ​ወ​ቱም ሳለ ድንቅ ተአ​ም​ራ​ትን አደ​ረገ፤ በሞ​ቱም ሥራው ድንቅ ነበረ።

15 ከዚ​ህም ሁሉ ጋር ሕዝቡ ንስሓ አል​ገ​ቡም፤ ከሀ​ገ​ራ​ቸ​ውም ተማ​ር​ከው እስ​ኪ​ሄዱ ድረስ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን አል​ተ​ዉም፤ በሀ​ገ​ሩም ሁሉ ተበ​ተኑ፤ ከሕ​ዝ​ቡም ጥቂት ሰዎች ቀሩ፤ ገዢም ከዳ​ዊት ቤት ቀረ።

16 ከእ​ነ​ር​ሱም ደግ ሥራ የሠሩ ነበሩ፤ ኀጢ​አ​ት​ንም ያበ​ዟት ነበሩ።


ንጉሡ ሕዝ​ቅ​ያስ

17 ሕዝ​ቅ​ያ​ስም ከተ​ማ​ውን አጸና በመ​ካ​ከ​ል​ዋም ውኃን አስ​ገባ፤ ዓለ​ቱ​ንም በብ​ረት ቈፈረ፤ የውኃ መስኖ አሠራ።

18 ሰና​ክ​ሬ​ምም በዘ​መኑ ዘመተ፤ ራፋ​ስ​ቂ​ስ​ንም ላከው፤ ወደ እር​ሱም ሄዶ በጽ​ዮን ላይ እጁን አነሣ፤ ታበየ፤ አፉ​ንም ከፍ ከፍ አድ​ርጎ ተና​ገረ።

19 ያን ጊዜም ልቡ​ና​ቸው ደነ​ገ​ጠ​ባ​ቸው፤ እጃ​ቸ​ውም ዛለ፤ እን​ደ​ም​ት​ወ​ልድ ሴትም ምጥ ያዛ​ቸው።

20 ይቅር ባይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ለመ​ኑት፤ እጃ​ቸ​ው​ንም ወደ እርሱ አነሡ፤ ቅዱ​ሱም ከሰ​ማይ ፈጥኖ ሰማ​ቸው፤ በኢ​ሳ​ይ​ያ​ስም እጅ አዳ​ና​ቸው።

21 የአ​ሦ​ር​ንም ሠራ​ዊት አጠፋ፤ መል​አ​ኩም አጠ​ፋ​ቸው።

22 ሕዝ​ቅ​ያስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኘው ሥራ ሠር​ት​ዋ​ልና፤ በራ​እዩ ታላ​ቅና ታማኝ የነ​በ​ረው ነቢዩ ኢሳ​ይ​ያ​ስም እን​ዳ​ዘ​ዘው የአ​ባቱ የዳ​ዊ​ትን መን​ገድ አጽ​ን​ት​ዋ​ልና።

23 ፀሐ​ይም በዘ​መኑ ከመ​ሄድ ወደ ኋላ ተመ​ለ​ሰች፤ ለን​ጉ​ሡም ዘመን ጨመ​ረ​ለት።

24 በታ​ላቅ መን​ፈ​ስም በመ​ጨ​ረሻ የሚ​ሆ​ነ​ውን አየ፤ በጽ​ዮን የሚ​ያ​ለ​ቅ​ሱ​ት​ንም አጽ​ና​ና​ቸው።

25 ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ የሚ​ሆ​ነ​ውን፥ የተ​ሰ​ወ​ረ​ው​ንም ሳይ​ሆን ተና​ገረ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos