Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ሲራክ 14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በአፉ ያል​ተ​ሰ​ነ​ካ​ከለ ሰው ብፁዕ ነው፤ ኀጢ​አ​ተኛ ሰውን ግን ኀዘን አያ​ስ​ደ​ነ​ግ​ጠ​ውም።

2 ሰው​ነ​ቱን የማ​ያ​ሳ​ዝን፥ ተስ​ፋ​ው​ንም የማ​ይ​ቈ​ርጥ ሰው ብፁዕ ነው።


ሀብ​ትን በሚ​ገባ ስለ መጠ​ቀም

3 ነገ​ርን ለማ​ያ​ውቅ ሰው ብል​ጽ​ግና አይ​ገ​ባ​ውም፤ ለን​ፉ​ግም ሰው ገን​ዘብ አይ​ገ​ባ​ውም።

4 ሰው​ነ​ቱን የሚ​ነ​ፍ​ጋት ሰው ለሌላ ያከ​ማ​ቻል፥ ሌላ ሰው ግን በገ​ን​ዘቡ ደስ ይለ​ዋል።

5 ሰው​ነ​ቱን የሚ​ነ​ፍግ በገ​ን​ዘ​ቡም ደስ የማ​ይ​ለው ሰው፥ ለማን ይለ​ግስ ዘንድ አለው?

6 ሰው​ነ​ቱን ከሚ​ነ​ፍግ ሰው የሚ​ከፋ የለም፤ ለክ​ፋ​ቱም እርሱ ፍዳ ይሆ​ነ​ዋል።

7 በጎ ቢያ​ደ​ር​ግም ባረጀ ጊዜ ብቻ ነው፥ ኋላም ክፋ​ቱን ያሳ​ው​ቃል።

8 የን​ፉግ ሰው ዐይኑ ክፉ ነው፥ ከድሃ ፊቱን የሚ​መ​ልስ ሰው​ነ​ቱን ቸል ይላል።

9 ለስሱ ሰው ዐይን ድር​ሻው አያ​ጠ​ግ​በ​ውም፤ የል​ቡ​ና​ውም ክፋት ሰው​ነ​ቱን ያከ​ሳ​ዋል።

10 የን​ፉግ ሰው ዐይኑ እህል ይነ​ፍ​ጋል፤ በማ​ዕ​ድም ይነ​ፍ​ጋል።

11 ልጄ ሆይ፥ የሚ​ቻ​ል​ህን ያህል ሰው​ነ​ት​ህን አዘ​ጋ​ጃት፥ እን​ደ​ሚ​ገ​ባ​ህም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መባእ አግባ።

12 ሞት እን​ደ​ማ​ይ​ቀር ዐስብ፥ የም​ት​ሞ​ት​ባ​ትም ቀን ትቀ​ራ​ለች ብለህ አት​ጠ​ራ​ጠር።

13 ሳት​ሞት ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ በጎ አድ​ርግ፤ እጅ​ህ​ንም ዘር​ግ​ተህ የተ​ቻ​ለ​ህን ያህል ስጥ።

14 በደ​ስ​ታህ ጊዜ አት​ታጣ፤ በጎ ድር​ሻ​ህም አያ​ም​ል​ጥህ።

15 ገን​ዘ​ብ​ህን ለባ​ዕድ የም​ት​ተው አይ​ደ​ለ​ምን? ወራ​ሾ​ች​ህስ ገን​ዘ​ብ​ህን ሁሉ የሚ​ካ​ፈሉ አይ​ደ​ለ​ምን?

16 ገን​ዘ​ብ​ህን አን​ሥ​ተህ ስጥ፥ ሰው​ነ​ት​ህ​ንም ደስ አሰ​ኛት፥ በመ​ቃ​ብር የም​ታ​ገ​ኘው ደስታ የለ​ምና።

17 ሰው ሁሉ እንደ ልብስ ያረ​ጃል፥ ሞትን ትሞት ዘንድ የሕግ ትእ​ዛዝ ተሠ​ር​ት​ዋ​ልና።

18 ቅጠሉ ጭፍቅ ያለ የእ​ን​ጨት ቅጠል የመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ቅጠል እን​ዲ​ረ​ግፍ የኋ​ላ​ውም እን​ዲ​ለ​መ​ልም፤ ደማ​ዊና ሥጋዊ ፍጥ​ረት ሁሉ እን​ዲሁ ነው፤ ይህ ይወ​ለ​ዳል ያም ይሞ​ታል።

19 ሥራ ሁሉ ፈጽሞ ይጠ​ፋል፤ ሠሪ​ውም ከሥ​ራው ጋር ይጠ​ፋል።


ጥበ​ብን በመ​ፈ​ለግ የሚ​ገኝ ደስታ

20 ነገር ግን ብልህ ሆኖ የሞተ፥ ጥበ​ቡ​ንም ተምሮ የጠ​በቀ ሰው ብፁዕ ነው።

21 የጥ​በ​ብን መን​ገድ በልቡ የሚ​ያ​ስብ፥ ምሥ​ጢ​ሯ​ንም የሚ​ማር፥

22 ጥበ​ብን የሚ​ከ​ተ​ላት፥ ፍለ​ጋ​ዋ​ንም የሚ​መ​ረ​ምር፥ መን​ገ​ድ​ዋ​ንም የሚ​ጠ​ብቅ፥

23 መስ​ኮ​ት​ዋን የሚ​ጎ​በኝ፥ በበ​ሮ​ች​ዋም ተቀ​ምጦ የሚ​ያ​ዳ​ምጥ፥

24 በቤ​ት​ዋም አጠ​ገብ የሚ​ኖር፥ በዙ​ሪ​ያ​ዋም የድ​ን​ኳ​ኑን ካስማ የሚ​ተ​ክል፥

25 ድን​ኳ​ኑን በአ​ጠ​ገ​ብዋ የሚ​ያ​ቆም፥ ባማረ ማደ​ሪ​ያ​ዋም የሚ​ኖር፥

26 ልጆ​ቹ​ንም በጥ​ላ​ዎ​ችዋ የሚ​ያ​ስ​ቀ​ምጥ፥ በቅ​ር​ን​ጫ​ፎ​ች​ዋም በታች የሚ​ያ​ድር፥

27 ከበ​ረሃ ሐሩ​ርም በበ​ታ​ችዋ የሚ​ጠ​ለል፤ በክ​ብ​ር​ዋም የሚ​ያ​ርፍ ብፁዕ ነው።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos