Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ልባም ሴትን ማን ያገ​ኛ​ታል? ዋጋው ብዙ ከሆነ ከከ​በረ ዕንቍ እጅግ የከ​በ​ረች ናት።

2 እን​ደ​ዚህ ባለ​ችዋ ሴት የባ​ልዋ ልብ ይታ​መ​ን​ባ​ታል፥ እን​ዲህ ያለ​ችው ሴትም ከመ​ል​ካም ምርኮ አታ​ሳ​ን​ሰ​ውም።

3 ዕድ​ሜ​ዋን ሙሉ በክፉ ላይ ክፉ ያይ​ደለ፥ በበጎ ላይ በጎ እየ​ሠ​ራች ባሏን ትረ​ዳ​ዋ​ለች።

4 የበግ ጠጕ​ር​ንና የተ​ልባ እግ​ርን እያ​ባ​ዘ​ተች፥ በእ​ጆ​ችዋ መል​ካም ትሠ​ራ​ለች።

5 እር​ስዋ ከሩቅ እን​ደ​ም​ት​ነ​ግድ፥ ሀብ​ት​ንም ሁሉ እን​ደ​ም​ት​ሰ​በ​ስብ መር​ከብ ናት፤

6 ገና ሌሊት ሳለ ትነ​ሣ​ለች፤ ለቤተ ሰዎ​ችዋ ምግ​ባ​ቸ​ውን ትሰ​ጣ​ለች። ለገ​ረ​ዶ​ች​ዋም ተግ​ባ​ራ​ቸ​ውን ትሰ​ጣ​ለች።

7 እር​ሻ​ንም ተመ​ል​ክታ ትገ​ዛ​ለች፤ ከእ​ጅ​ዋም ፍሬ ወይ​ንን ትተ​ክ​ላ​ለች።

8 ወገ​ብ​ዋ​ንም በኀ​ይል ትታ​ጠ​ቃ​ለች፥ እጆ​ች​ዋ​ንም ለሥራ ታወ​ጣ​ለች።

9 ሥራ መል​ካም እንደ ሆነ ትመ​ለ​ከ​ታ​ለች፤ መብ​ራቷ ሌሊ​ቱን ሁሉ አይ​ጠ​ፋም።

10 እጆ​ች​ዋ​ንም ወደ​ሚ​ጠ​ቅም ሥራ ትዘ​ረ​ጋ​ለች፥ ክን​ድ​ዋ​ንም ለመ​ፍ​ተል ታበ​ረ​ታ​ለች።

11 እጅ​ዋን ለች​ግ​ረኛ ትዘ​ረ​ጋ​ለች፥ መሀል እጅ​ዋ​ንም ወደ ድሃ ትዘ​ረ​ጋ​ለች።

12 ባሏ በውጭ የዘ​ገየ እንደ ሆነ በቤት ስላ​ሉት ምንም አያ​ስ​ብም ። ቤተ ሰዎ​ችዋ ሁሉ እጥፍ ድርብ የለ​በሱ ናቸ​ውና።

13 ለባሏ እጥፍ ሆኖ ከተ​ፈ​ተለ የተ​ልባ እግር መጐ​ና​ጸ​ፊያ ትሠ​ራ​ለች፤ ለራ​ስ​ዋም ከነጭ ሐር ልብ​ስን ትሠ​ራ​ለች።

14 ባልዋ በሀ​ገር ሽማ​ግ​ሌ​ዎች መካ​ከል በሸ​ንጎ በተ​ቀ​መጠ ጊዜ፥ በአ​ደ​ባ​ባይ የታ​ወቀ ይሆ​ናል።

15 የበ​ፍታ ቀሚስ እየ​ሠ​ራች ትሸ​ጣ​ለች። ለከ​ነ​ዓ​ና​ው​ያ​ንም ድግ ትሸ​ጣ​ለች። ሕጋዊ በሆነ ነገር አፍ​ዋን ትከ​ፍ​ታ​ለች፤ ለአ​ን​ደ​በ​ቷም መጠ​ንን ታደ​ር​ጋ​ለች።

16 ብር​ታ​ት​ንና ውበ​ትን ትለ​ብ​ሳ​ለች፤ በኋ​ላም ዘመን ላይ ደስ ይላ​ታል።

17 ወደ ቤትዋ የሚ​ገባ ብዙ ነው፥ የስ​ን​ፍና እን​ጀ​ራ​ንም አት​በ​ላም።

18 ሕግና ምጽ​ዋት በአ​ፍዋ አለ፥ አፍ​ዋን በጥ​በ​ብና ሕግ ባለው ሥር​ዐት ትከ​ፍ​ታ​ለች።

19 ምጽ​ዋቷ ልጆ​ች​ዋን ያሳ​ድ​ጋል፥ ያበ​ለ​ጥ​ጋ​ልም፤ ባል​ዋም እን​ዲህ ሲል ያመ​ሰ​ግ​ና​ታል፦

20 “ብዙ ሴቶች ልጆች ሀብ​ትን ሰበ​ሰቡ፤ ብዙ​ዎ​ቹም ኀይ​ልን አደ​ረጉ፤ አንቺ ግን ትበ​ል​ጫ​ለሽ፥ ከሁ​ሉም ትል​ቂ​ያ​ለሽ።”

21 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም​ግ​ባ​ትም ከንቱ ነው፤ ብልህ ሴት ግን ትባ​ረ​ካ​ለች። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም የም​ት​ፈራ እር​ስዋ ትመ​ሰ​ገ​ና​ለች።

22 ከከ​ን​ፈሯ ፍሬ ስጡ​አት፥ ባሏም በአ​ደ​ባ​ባይ ይመ​ሰ​ገ​ናል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos