Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa መጽሐፈ ተግሣጽ 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)1 አንገቱን ካደነደነ ሰው ይልቅ፥ የሚዘልፍ ሰው ይሻላል። ድንገት ይቃጠላልና፥ፈውስም የለውምና። 2 በጻድቃን መመስገን ሕዝቦች ደስ ይላቸዋል፤ ክፉዎች ገዢዎች በሚሆኑበት ጊዜ ግን ሰዎች ያለቅሳሉ። 3 ጥበብን በሚወድድ ልጅ አባቱ ደስ ይለዋል፤ ጋለሞቶችን የሚከተል ግን ሀብቱን ያጠፋል። 4 እውነተኛ ንጉሥ ሀገሩን ያጸናል፤ ዐመፀኛ ሰው ግን ያፈርሰዋል። 5 በወዳጁ ፊት ወጥመድን የሚያዘጋጅ ሰው የራሱን እግሮች በውስጡ ያገባል። 6 በክፉ ሰው ዐመፃ ወጥመድ ይበዛል፤ ኀጢአተኛ ሰውም በታላቅ ወጥመድ ይወድቃል፥ ጻድቅ ግን በደስታና በሐሴት ይኖራል። 7 ጻድቅ የድሆችን ፍርድ ይመለከታል፤ ኃጥእ ግን ዕውቀትን አያስተውልም። ለድሃም ዕውቀት ያለው ልቡና የለውም። 8 ክፉዎች ሰዎች ከተማን ያቃጥላሉ፤ ጠቢባን ግን ቍጣን ይመልሳሉ። 9 ጠቢብ ሰው ሕዝብን ይገዛል፥ ክፉ ሰው ግን ይቈጣል፥ ይሥቁበታልም፥ ነገር ግን አያሳዝነውም። 10 ደምን ለማፍሰስ የሚተባበሩ ሰዎች ጻድቁን ሰው ይጠላሉ፥ ቅኖች ግን ነፍሱን ይሻሉ። 11 አላዋቂ ሰው ቍጣውን ሁሉ ያወጣል፤ ጠቢብ ሰው ግን ድርሻውን እንኳ በከፊል ያስቀረዋል። 12 ንጉሥ ሐሰተኛ ነገርን ቢያደምጥ፥ በእርሱ በታች ያሉት ሁሉ ዐመፀኞች ይሆናሉ። 13 አበዳሪና ተበዳሪ በተገናኙ ጊዜ እግዚአብሔር ሁለቱን በአንድነት ይጐበኛቸዋል። 14 ለድሆች በእውነት የሚፈርድ ንጉሥ፥ ዙፋኑ ለዘለዓለም ይጸናል። 15 በትርና ተግሣጽ ጥበብን ይሰጣሉ፤ ስሕተተኛ ብላቴና ግን ቤተ ሰቦቹን ያሳፍራል። 16 ኃጥኣን ሲበዙ ኀጢአት ትበዛለች፤ ጻድቃን ግን በክፉዎች ውድቀት ይፈራሉ። 17 ልጅህን ቅጣ፥ ዕረፍትንም ይሰጥሃል፤ ለነፍስህም ክብርን ይሰጣታል። 18 ለኀጢአተኛ ሕዝብ አስተማሪ የለውም፤ ሕግን የሚጠብቅ ግን ብፁዕ ነው። 19 ክፉ አገልጋይ በቃል አይገሠጽም፤ ቢያውቅ እንኳ አይታዘዝምና። 20 በቃሉ የሚቸኩለውን ሰው ብታይ፥ ከእርሱ ይልቅ ለአላዋቂ ተስፋ እንዳለ ዕወቅ። 21 ቸልተኛ ሰው ከሕፃንነቱ ጀምሮ አገልጋይ ይሆናል፤ በኋላ ግን ራሱን ያሳዝናል። 22 ቍጡ ሰው ጠብን ይጭራል፥ ወፈፍተኛ ሰውም ኀጢአትን ያበዛል። 23 ትዕቢት ሰውን ያዋርደዋል፥ ሕሊናውን የሚያዋርደውን ሰው ግን እግዚአብሔር ለክብር ያቀርበዋል። 24 ከሌባ ጋር የሚካፈል ነፍሱን ይጠላል፤ መሐላንም ቢያወርዱለት ይምላል፤ አይናገርምም። 25 በመፍራትና በማፈር ሰው ይሰነካከላል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን ደስ ይለዋል። የሰው ኀጢአቱ በደለኛ ያሰኘዋል፥ በእግዚአብሔር የታመነ ሰው ግን ይድናል። 26 ብዙ ሰዎች ለመኳንንት ፊት ይላላካሉ፤ የሰው ፍርዱ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። 27 እውነተኛ ሰው በግፈኛ ሰው ዘንድ የተናቀ ነው፤ ቀና መንገድም በኃጥኣን ዘንድ አስጸያፊ ነው። |