Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የይ​ሁዳ ንጉሥ የሕ​ዝ​ቅ​ያስ ወዳ​ጆች ያለ ጥር​ጥር የጻ​ፉት የተ​ለ​ያየ የሰ​ሎ​ሞን ተግ​ሣጽ ነው።

2 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር ነገ​ርን ይሰ​ው​ራል፥ የን​ጉሥ ክብር ግን ነገ​ርን ያከ​ብ​ራል።

3 ሰማይ ከፍ ያለ ነው፥ ምድ​ርም ጥልቅ ነው፥ የን​ጉሥ ልብም እን​ዲሁ አይ​ታ​ወ​ቅም።

4 ያል​ጠ​ራ​ውን ብር አጥ​ራው፥ ፈጽ​ሞም ይጠ​ራል።

5 ከን​ጉሡ ፊት ክፉ​ዎ​ችን አጥፋ፥ ዙፋ​ኑም በጽ​ድቅ ይቀ​ናል።

6 በን​ጉሥ ፊት አት​ታ​በይ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት አት​መ​ጻ​ደቅ፥ በመ​ኳ​ን​ንት ስፍራ አት​ቁም፤

7 በመ​ኰ​ንን ፊት ከም​ቷ​ረድ፦ ወደ​ዚህ ከፍ በል ብት​ባል ይሻ​ል​ሃ​ልና፥ ዐይ​ኖ​ችህ ያዩ​ትን ተና​ገር።

8 ኋላ እን​ዳ​ት​ጸ​ጸት፥ ለጥል ፈጥ​ነህ አት​ውጣ። ክር​ክ​ርን ከባ​ል​ን​ጀ​ራህ ጋር ተከ​ራ​ከር፥ ምሥ​ጢ​ሩ​ንም አት​ግ​ለጥ።

9 ባል​ን​ጀ​ራህ በነ​ቀ​ፈህ ጊዜ ወደ​ኋ​ላህ ተመ​ለስ፥ ባል​ን​ጀ​ራ​ህም እን​ዳ​ይ​ነ​ቅ​ፍህ ቸል አት​በ​ለው፥ ጠብ​ህም ክር​ክ​ር​ህም ከእ​ርሱ አያ​ር​ቅ​ህም።

10 ምሥ​ጢ​ሩን ብት​ገ​ልጥ ግን የሞት ያህል ይሆ​ን​ብ​ሃል፥ ጸጋና ወን​ድ​ማ​ማ​ች​ነ​ትም ነጻ ያደ​ር​ጋል። ነገር ግን መዘ​ባ​በቻ እን​ዳ​ት​ሆን ራስ​ህን ጠብቅ፤ በመ​ል​ካም ሥራ​ህም መን​ገ​ዶ​ች​ህን ጠብቅ።

11 በብር ጻሕል ላይ ያለ የወ​ርቅ ዕን​ኰይ ያማረ እን​ደ​ሚ​ሆን፥ በየ​መ​ልኩ የሚ​ና​ገ​ሩት ቃልም እን​ዲሁ ነው።

12 በወ​ርቅ ጉትቻ ላይ ያለ ዋጋው ብዙ የሆነ ሰር​ድ​ዮን የሚ​ባል የዕ​ንቍ ፈርጥ ያማረ እን​ደ​ሆነ፥ እን​ደ​ዚሁ የብ​ልህ ነገር በሚ​ሰማ ሰው ጆሮ ያማረ ነው።

13 በመ​ከር ወራት በቈላ የው​ርጭ ጠል ደስ እን​ደ​ሚ​ያ​ሰኝ፥ እን​ዲሁ የታ​መነ መል​እ​ክ​ተኛ ለላ​ኩት ይጠ​ቅ​ማል። የጌ​ቶ​ቹን ነፍስ ያሳ​ር​ፋ​ልና።

14 በሐ​ሰ​ተኛ ሀብት የሚ​መኩ ሁሉ፥ ዝናብ እን​ደ​ሌ​ላ​ቸው ደመ​ና​ትና ነፋ​ሳት ናቸው።

15 የሕ​ይ​ወት ውበት በት​ዕ​ግ​ሥት ትነ​ግ​ሣ​ለች፥ ልዝብ አን​ደ​በ​ትም አጥ​ን​ትን ትሰ​ብ​ራ​ለች።

16 ልጄ ሆይ፥ አጥ​ብ​ቀህ እን​ዳ​ት​ጠ​ግብ፥ እን​ዳ​ት​ተ​ፋ​ውም ማር ባገ​ኘህ ጊዜ በልኩ ብላ።

17 እን​ዳ​ይ​ሰ​ለ​ችህ እን​ዳ​ይ​ጠ​ላ​ህም፥ እግ​ር​ህን ወደ ባል​ጀ​ራህ ቤት አታ​ዘ​ው​ትር።

18 በባ​ል​ጀ​ራው ላይ በሐ​ሰት የሚ​መ​ሰ​ክር፥ እንደ በት​ርና እንደ ሰይፍ እንደ ተሳ​ለም ፍላጻ ነው።

19 የክፉ መን​ገ​ድና የኀ​ጢ​አ​ተኛ እግር፥ በክፉ ቀን ይጠ​ፋሉ።

20 መጻጻ ለቍ​ስል እን​ደ​ማ​ይ​መች፥ እን​ደ​ዚ​ሁም በሥጋ ላይ የሚ​ወ​ርድ ነውር ልብን ያሳ​ዝ​ናል። ነቀዝ ዕን​ጨ​ትን፥ ብልም ልብ​ስን እን​ደ​ሚ​በ​ላው፥ እን​ደ​ዚሁ ኀዘን የሰ​ውን ልብ ትጐ​ዳ​ለች።

21 ጠላ​ትህ ቢራብ አብ​ላው፥ ቢጠ​ማም አጠ​ጣው።

22 ይህን ብታ​ደ​ርግ በራሱ ላይ ፍም ትሰ​በ​ስ​ባ​ለህ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መል​ካም ዋጋ​ህን ይመ​ል​ስ​ል​ሃል።

23 የሰ​ሜን ነፋስ ወጀብ ያመ​ጣል፤ ፊትን የማ​ያ​ፍር ምላ​ስም ያስ​ቈ​ጣል።

24 ከነ​ዝ​ናዛ ሴት ጋር ባማረ ቤት ከመ​ቀ​መጥ፥ አንድ ጎኑ በፈ​ረሰ ግንብ መቀ​መጥ ይሻ​ላል።

25 የቀ​ዘ​ቀዘ ውኃ ለተ​ጠ​ማች ሰው​ነት መል​ካም እንደ ሆነ፥ ከሩቅ ሀገር የመጣ የም​ሥ​ራ​ችም እን​ዲሁ መል​ካም ነው።

26 በኃ​ጥ​ኣን ፊት የጻ​ድቅ መው​ደቅ፥ ጕድ​ጓ​ድን እንደ መዝ​ጋ​ትና የውኃ መው​ጫን እንደ ማጥ​ፋት ነው።

27 ብዙ ማር መብ​ላት መል​ካም አይ​ደ​ለም፤ እን​ዲ​ሁም የራ​ስን ክብር መፈ​ለግ አያ​ስ​ከ​ብ​ርም።

28 ቅጥር እን​ደ​ሌ​ላት እንደ ፈረ​ሰች ከተማ፥ ያለ ምክር የሚ​ኖር ሰው እን​ዲሁ ነው።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos