Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 75 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ በበ​ገ​ና​ዎች ስለ አሦ​ራ​ው​ያን የአ​ሳፍ የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በይ​ሁዳ ታወቀ፥ ስሙም በእ​ስ​ራ​ኤል ታላቅ ሆነ።

2 በሀ​ገ​ሩም በሰ​ላም ኖረ፥ ማደ​ሪ​ያ​ውም በጽ​ዮን ነው፤

3 በዚ​ያም የቀ​ስ​ትን ኀይል፥ ጋሻን፥ ጦር​ንና ሰል​ፍ​ንም ሰበረ፤ በዚ​ያም ቀን​ዶ​ችን ሰበረ።

4 አንተ በዘ​ለ​ዓ​ለም ተራ​ሮች ሆነህ በድ​ንቅ ታበ​ራ​ለህ።

5 ልበ ሰነ​ፎች ሁሉ ደነ​ገጡ፥ ሕል​ምን አለሙ፥ ያገ​ኙት ግን የለም፤ ሰው ሁሉ ለእጁ ባለ​ጠ​ግ​ነት ነው።

6 የያ​ዕ​ቆብ አም​ላክ ሆይ፥ ከተ​ግ​ሣ​ጽህ የተ​ነሣ ፈረ​ሰ​ኞች ሁሉ አን​ቀ​ላፉ።

7 አንተ ግን፥ ግሩም ነህ፤ ቍጣ​ህን ማን ይቃ​ወ​ማል?

8 ፍር​ድን ከሰ​ማይ ታሰ​ማ​ለህ። ምድር ፈራች፥ ዝምም አለች፥

9 ልበ የዋ​ሃ​ንን ሁሉ ያድን ዘንድ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለፍ​ርድ በተ​ነሣ ጊዜ።

10 ሰው በፈ​ቃዱ ያመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ልና፥ ከሕ​ሊ​ና​ቸው ትር​ፍም በዓ​ል​ህን ያደ​ር​ጋሉ።

11 ለአ​ም​ላ​ካ​ችን ለአ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስእ​ለ​ትን ሰጡ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ያሉ ሁሉ እጅ መን​ሻን ለሚ​ያ​ስ​ፈ​ራው ያገ​ባሉ።

12 የአ​ለ​ቆ​ችን ነፍስ ያወ​ጣል፤ በም​ድ​ርም ነገ​ሥ​ታት ዘንድ ያስ​ፈ​ራል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos