Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 59 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ የሶ​ር​ያን ሁለ​ቱን ወን​ዞ​ችና የሶ​ር​ያን ሶባ​ልን ባቃ​ጠለ ጊዜ ኢዮ​አ​ብም ተመ​ልሶ ከኤ​ዶ​ማ​ው​ያን ሰዎች በጨው ሸለቆ ዐሥራ ሁለት ሺህ ሰዎ​ችን በገ​ደለ ጊዜ ለት​ም​ህ​ርት የዳ​ዊት ቅኔ።

1 አቤቱ፥ ጣል​ኸን አፈ​ረ​ስ​ኸ​ንም፤ ገረ​ፍ​ኸን፥ ይቅ​ርም አል​ኸን።

2 ምድ​ርን አና​ወ​ጥ​ሃት፥ አወ​ክ​ሃ​ትም፤ ተና​ው​ጣ​ለ​ችና ቍስ​ል​ዋን ፈወ​ስ​ኻት።

3 ለሕ​ዝ​ብህ ጭን​ቅን አሳ​የ​ሃ​ቸው፥ አስ​ደ​ን​ጋ​ጩ​ንም ወይን አጠ​ጣ​ኸን።

4 ለሚ​ፈ​ሩህ ምል​ክ​ትን ሰጠ​ሃ​ቸው፥ ከቀ​ስት ፊት ያመ​ልጡ ዘንድ።

5 ወዳ​ጆ​ች​ህም፥ እን​ዲ​ድኑ በቀ​ኝህ አድን፥ ስማ​ኝም።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ቅ​ደሱ ተና​ገረ፤ ደስ ይለ​ኛል፥ ምር​ኮ​ንም እካ​ፈ​ላ​ለሁ፥ የሸ​ለቆ ቦታ​ዎ​ችን እሰ​ፍ​ራ​ለሁ።

7 ገለ​ዓድ የእኔ ነው፥ ምና​ሴም የእኔ ነው፤ ኤፍ​ሬም የራሴ መጠ​ጊያ ነው። ይሁዳ ንጉሤ ነው፤

8 ካህን ሞአ​ብም ተስ​ፋዬ ነው በኤ​ዶ​ም​ያስ ላይ ጫማ​ዬን እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ምም ይገ​ዙ​ል​ኛል።

9 ቅጥር ወደ አለ​ባት ወደ ጽኑ ከተማ ማን ይወ​ስ​ደ​ኛል? ማንስ እስከ ኤዶ​ም​ያስ ይመ​ራ​ኛል?

10 አቤቱ፥ የጣ​ል​ኸን አንተ አይ​ደ​ለ​ህ​ምን? አም​ላ​ካ​ችን ሆይ፥ ከሠ​ራ​ዊ​ታ​ችን ጋር አት​ወ​ጣም።

11 በመ​ከ​ራ​ችን ረድ​ኤ​ትን ስጠን፥ በሰ​ውም መታ​መን ከንቱ ነው።

12 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀይ​ልን እና​ደ​ር​ጋ​ለን፤ እር​ሱም የሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቁ​ንን ያዋ​ር​ዳ​ቸ​ዋል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos