Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 54 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ በበ​ገ​ና​ዎች የዳ​ዊት ትም​ህ​ርት።

1 አቤቱ፥ ጸሎ​ቴን አድ​ም​ጠኝ፥ ልመ​ና​ዬ​ንም ቸል አት​በ​ለኝ።

2 ተመ​ል​ከ​ተኝ፥ ስማ​ኝም፤ አዘ​ንሁ፥ ደነ​ገ​ጥሁ፥ ተና​ወ​ጥ​ሁም፤

3 ከጠ​ላት ድምፅ፥ ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኛም ማሠ​ቃ​የት የተ​ነሣ፥ ዐመ​ፃን በላዬ መል​ሰ​ው​ብ​ኛ​ልና፥ ሊያ​ጠ​ፉ​ኝም ተነ​ሥ​ተ​ው​ብ​ኛ​ልና።

4 ልቤ በላዬ ደነ​ገ​ጠ​ብኝ፥ የሞት ድን​ጋ​ጤም መጣ​ብኝ።

5 ፍር​ሃ​ትና እን​ቅ​ጥ​ቅጥ ያዙኝ፥ ጨለ​ማም ሸፈ​ነኝ።

6 በርሬ ዐርፍ ዘንድ እንደ ርግብ ክን​ፍን ማን በሰ​ጠኝ አልሁ፥

7 እነሆ፥ ኮብ​ልዬ በራ​ቅሁ፥ በም​ድረ በዳም በኖ​ርሁ፤

8 እንደ ዐውሎ ነፋስ ከሆ​ነው ከነ​ፍሴ መቅ​በ​ዝ​በዝ የሚ​ያ​ድ​ነ​ኝን ተስፋ አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ።

9 አቤቱ፥ ዐመ​ፃ​ንና ጠብን በከ​ተማ ውስጥ አይ​ች​አ​ለ​ሁና አስ​ጥ​ማ​ቸው፥ አን​ደ​በ​ታ​ቸ​ው​ንም ቍረጥ።

10 በቀ​ንና በሌ​ሊት በቅ​ጥ​ርዋ ይከ​ብ​ቡ​አ​ታል፤ ዐመ​ፃና ድካም ኀጢ​አ​ትም በመ​ካ​ከ​ልዋ ነው፤

11 ሽን​ገላ ከአ​ደ​ባ​ባ​ይዋ አይ​ር​ቅም።

12 ጠላ​ትስ ቢሰ​ድ​በኝ፥ በታ​ገ​ሥሁ ነበር፤ የሚ​ጠ​ላ​ኝም አፉን በላዬ ከፍ ከፍ ቢያ​ደ​ርግ፥ ከእ​ርሱ በተ​ሸ​ሸ​ግሁ ነበር።

13 አንተ ሰው፥ አንተ ግን እንደ ራሴ ነበ​ርህ፥ ባል​ን​ጀ​ራ​ዬና የማ​ው​ቅህ ወዳ​ጄም ነበ​ርህ፤

14 መብ​ልን ከእኔ ጋር በአ​ን​ድ​ነት ያጣ​ፈ​ጥህ ነበ​ርህ፤ በአ​ንድ ልብ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ተራ​መ​ድን።

15 ሞት ይም​ጣ​ባ​ቸው፤ በሕ​ይ​ወት ሳሉም ወደ ሲኦል ይው​ረዱ፤ ክፋት በማ​ደ​ሪ​ያ​ቸ​ውና በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ነውና።

16 እኔ ግን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኽሁ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰማኝ።

17 በማ​ታና በጥ​ዋት በቀ​ት​ርም እና​ገ​ራ​ለሁ አስ​ረ​ዳ​ለሁ፥ ቃሌ​ንም አይ​ሰ​ሙ​ኝም።

18 ከእኔ ጋር ካሉት ይበ​ዛ​ሉና ከሚ​ቃ​ረ​ቡኝ ነፍ​ሴን በሰ​ላም አድ​ናት።

19 ቤዛ የላ​ቸ​ው​ምና፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አል​ፈ​ሩ​ት​ምና ዓለም ሳይ​ፈ​ጠር የነ​በረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰምቶ ያጐ​ሰ​ቍ​ላ​ቸ​ዋል።

20 ፍዳን ለማ​ም​ጣት እጁን ዘረጋ፤ ኪዳ​ኑ​ንም አረ​ከሱ።

21 ከፊ​ቱም ቍጣ የተ​ነሣ ተለ​ያዩ፥ ልቡም ቀረበ፤ ቃሉም ከቅቤ ይልቅ ለሰ​ለሰ፤ እነ​ርሱ ግን እን​ደ​ሚ​ያ​ሰ​ጥም ማዕ​በል ናቸው።

22 ትካ​ዜ​ህን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላይ ጣል፥ እር​ሱም ይመ​ግ​ብ​ሃል፤ ለጻ​ድ​ቁም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሁከ​ትን አይ​ሰ​ጠ​ውም።

23 አንተ ግን፥ አቤቱ፥ ወደ ሞት ጕድ​ጓድ አው​ር​ዳ​ቸው፤ የደም ሰዎ​ችና ሸን​ጋ​ዮች ዘመ​ና​ቸ​ውን አያ​ጋ​ም​ሱም፤ እኔ ግን፥ አቤቱ እታ​መ​ን​ሃ​ለሁ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos