Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 48 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ የቆሬ ልጆች መዝ​ሙር።

1 አሕ​ዛብ ሁላ​ችሁ፥ ይህን ስሙ፤ በዓ​ለም የም​ት​ኖ​ሩም ሁላ​ችሁ፥ አድ​ምጡ፤

2 የሰው ልጆች ባለ​ጠ​ጎ​ችና ድሆች፥ በየ​ሀ​ገ​ራ​ችሁ በአ​ን​ድ​ነት።

3 አፌ ጥበ​ብን ይና​ገ​ራል፥ የል​ቤም ዐሳብ ምክ​ርን፥

4 በጆ​ሮዬ ምሳሌ አደ​ም​ጣ​ለሁ፥ በበ​ገ​ናም ነገ​ሬን እገ​ል​ጣ​ለሁ።

5 ከክፉ ቀን ለምን እፈ​ራ​ለሁ? ኀጢ​አት ተረ​ከ​ዜን ከበ​በኝ፤

6 በኀ​ይ​ላ​ቸው የሚ​ታ​መኑ፥ በባ​ለ​ጠ​ግ​ነ​ታ​ቸ​ውም ብዛት የሚ​ኮሩ፤

7 ወን​ድም ወን​ድ​ሙን አያ​ድ​ንም፥ ሰውም አያ​ድ​ንም፤ ቤዛ​ው​ንም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አይ​ሰ​ጥም፥

8 የነ​ፍ​ሱ​ንም ዋጋ ለውጥ፥

9 በዓ​ለም የደ​ከመ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይድ​ናል፥ ጥፋ​ትን አያ​ይ​ምና።

10 ጠቢ​ባ​ንን ሲሞቱ ባየ​ሃ​ቸው ጊዜ፥ እን​ደ​ዚሁ ልብ የሌ​ላ​ቸው ሰነ​ፎች ይጠ​ፋሉ፥ ገን​ዘ​ባ​ቸ​ው​ንም ለሌ​ሎች ይተ​ዋሉ።

11 መቃ​ብ​ራ​ቸው ለዘ​ለ​ዓ​ለም ቤታ​ቸው ነው፥ ማደ​ሪ​ያ​ቸ​ውም ለልጅ ልጅ ነው፤ በየ​ሀ​ገ​ራ​ቸ​ውም ስማ​ቸው ይጠ​ራል።

12 ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አላ​ወ​ቀም፤ ልብ እን​ደ​ሌ​ላ​ቸው እን​ስ​ሶ​ችም ሆነ፥ መሰ​ላ​ቸ​ውም።

13 በአ​ፋ​ቸው ሲወዱ፥ ራስዋ መን​ገ​ዳ​ቸው መሰ​ና​ክ​ላ​ቸው ናት፥

14 እንደ በጎች ሞት በሲ​ኦል ይጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋል፥ ቅኖ​ችም በማ​ለዳ ይገ​ዙ​አ​ቸ​ዋል፥ ረድ​ኤ​ታ​ቸ​ውም ከክ​ብ​ራ​ቸው ተለ​ይታ በሲ​ኦል ትጠ​ፋ​ለች።

15 ነገር ግን በሚ​ወ​ስ​ዱኝ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነፍ​ሴን ከሲ​ኦል እጅ ያድ​ና​ታል።

16 በበ​ለ​ጸገ ጊዜ፥ የቤ​ቱም ክብር በበዛ ጊዜ ሰውን አት​ፍ​ራው፥

17 በሚ​ሞት ጊዜ ከእ​ርሱ ጋር ምንም አይ​ወ​ስ​ድ​ምና፥ የቤ​ቱም ክብር ሁሉ ከእ​ርሱ ጋር አይ​ወ​ር​ድ​ምና።

18 በሕ​ይ​ወቱ ሳለ ሰው​ነቱ ደስ ብሎ​አ​ታ​ልና ሰው መል​ካም ብታ​ደ​ር​ግ​ለት ያመ​ሰ​ግ​ን​ሃል።

19 ወደ አባ​ቶ​ቹም ዓለም ይወ​ር​ዳል፤ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ብር​ሃ​ንን አያ​ይም።

20 ሰው ግን ክቡር ሲሆን አላ​ወ​ቀም። ልብ እን​ደ​ሌ​ላ​ቸው እን​ስ​ሶ​ችም ሆነ፥ መሰ​ላ​ቸ​ውም።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos