Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 47 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


በሁ​ለ​ተኛ ሰን​በት ማግ​ሥት የቆሬ ልጆች የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታላቅ ነው፤ በአ​ም​ላ​ካ​ችን ከተማ በመ​ቅ​ደሱ ተራራ ምስ​ጋ​ናው ብዙ ነው።

2 ለም​ድር ሁሉ ደስ​ታን የሚ​ያ​ዝዝ፥ የጽ​ዮን ተራ​ራ​ዎች በመ​ስዕ በኩል ናቸው። የታ​ላቁ ንጉሥ ከተማ ናት።

3 በተ​ቀ​በ​ሏት ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በረ​ከ​ት​ዋን ያው​ቃል

4 እነሆ፥ የም​ድር ነገ​ሥ​ታት ተሰ​ብ​ስ​በው በአ​ን​ድ​ነት መጥ​ተ​ዋል።

5 እነ​ር​ሱስ ይህን አይ​ተው አደ​ነቁ፥ ደነ​ገጡ፥ ፈሩም።

6 መን​ቀ​ጥ​ቀ​ጥም ያዛ​ቸው፥ እንደ ወላ​ድም በዚያ አማጡ።

7 በኀ​ይ​ለኛ ነፋስ የተ​ር​ሴ​ስን መር​ከ​ቦች ትቀ​ጠ​ቅ​ጣ​ቸ​ዋ​ለህ።

8 እን​ደ​ሰ​ማን እን​ዲሁ አየን፥ በሠ​ራ​ዊት ጌታ ከተማ፥ በአ​ም​ላ​ካ​ችን ከተማ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያጸ​ና​ታል።

9 አም​ላክ ሆይ፥ በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ይቅ​ር​ታ​ህን ተቀ​በ​ልን።

10 አም​ላክ ሆይ፥ እንደ ስምህ እን​ዲ​ሁም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስ​ጋ​ናህ ነው። ቀኝህ ጽድ​ቅን የተ​መላ ነው።

11 አቤቱ፥ ስለ ፍር​ድህ የጽ​ዮን ተራ​ሮች ደስ ይላ​ቸ​ዋል፥ የይ​ሁ​ዳም ሴቶች ልጆች ሐሤት ያደ​ር​ጋሉ።

12 ጽዮ​ንን ክበ​ቡ​አት፥ ዕቀ​ፉ​አ​ትም። በቅ​ጥ​ሮ​ች​ዋም ተና​ገሩ፤

13 በብ​ር​ታቷ ልባ​ች​ሁን አኑሩ፤ በረ​ከ​ቷ​ንም ትካ​ፈ​ላ​ላ​ችሁ ለሚ​መ​ጣ​ውም ትው​ልድ ትነ​ግሩ ዘንድ።

14 ለዓ​ለ​ምና ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይህ አም​ላ​ካ​ችን እንደ ሆነ፥ እር​ሱም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይጠ​ብ​ቀ​ናል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos