Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 33 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ባሳ​ደ​ደው በአ​ቤ​ሜ​ሌክ ፊት መል​ኩን በለ​ወጠ ጊዜ፥ በሄ​ደም ጊዜ የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሁል​ጊዜ አመ​ሰ​ግ​ነ​ዋ​ለሁ። ምስ​ጋ​ና​ውም ዘወ​ትር በአፌ ነው።

2 ነፍ​ሴም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትከ​ብ​ራ​ለች፥ ገሮ​ችም ይስሙ፥ ደስም ይበ​ላ​ቸው።

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከእኔ ጋር ከፍ ከፍ አድ​ር​ጉት፥ በአ​ን​ድ​ነ​ትም ስሙን ከፍ ከፍ እና​ድ​ርግ።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈለ​ግ​ሁት መለ​ሰ​ል​ኝም፥ ከመ​ከ​ራ​ዬም ሁሉ አዳ​ነኝ።

5 ወደ እርሱ ቅረቡ ያበ​ራ​ላ​ች​ሁ​ማል፥ ፊታ​ች​ሁም አያ​ፍ​ርም።

6 ይህ ችግ​ረኛ ጮኸ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰማው፥ ከመ​ከ​ራ​ውም ሁሉ አዳ​ነው።

7 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ በሚ​ፈ​ሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰ​ፍ​ራል፥ ያድ​ና​ቸ​ው​ማል።

8 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ፥ ዕወ​ቁም፤ በእ​ርሱ የሚ​ታ​መን ሰው ብፁዕ ነው።

9 ለሚ​ፈ​ሩት ችግር የለ​ባ​ቸ​ው​ምና ቅዱ​ሳን ሁሉ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍሩት።

10 ባለ​ጠ​ጎች ደኸዩ፥ ተራ​ቡም፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈ​ል​ጉት ግን ከመ​ል​ካም ነገር ሁሉ አል​ተ​ቸ​ገ​ሩም።

11 ልጆቼ ኑ፥ ስሙኝ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት አስ​ተ​ም​ራ​ችሁ ዘንድ፤

12 ሕይ​ወ​ትን የሚ​ፈ​ቅድ ሰው ማን ነው? በጎ ዘመ​ን​ንም ለማ​የት የሚ​ወ​ድድ ማን ነው?

13 አን​ደ​በ​ት​ህን ከክፉ ከል​ክል፥ ከን​ፈ​ሮ​ች​ህም ሽን​ገ​ላን እን​ዳ​ይ​ና​ገሩ።

14 ከክፉ ሽሽ፥ መል​ካ​ም​ንም አድ​ርግ፤ ሰላ​ምን ሻት፥ ተከ​ተ​ላ​ትም።

15 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዐይ​ኖች ወደ ጻድ​ቃኑ፥ ጆሮ​ቹም ወደ ልመ​ና​ቸው ናቸ​ውና።

16 መታ​ሰ​ቢ​ያ​ቸ​ውን ከም​ድር ያጠፋ ዘንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉን በሚ​ያ​ደ​ርጉ ላይ ነው።

17 ጻድ​ቃን ጮኹ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰማ​ቸው፥ ከመ​ከ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ አዳ​ና​ቸው።

18 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በል​ባ​ቸው የዋ​ሃን ለሆኑ ቅርብ ነው፥ በመ​ን​ፈስ ትሑ​ታን የሆ​ኑ​ት​ንም ያድ​ና​ቸ​ዋል።

19 የጻ​ድ​ቃን መከ​ራ​ቸው ብዙ ነው፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከሁሉ ያድ​ና​ቸ​ዋል።

20 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አጥ​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ሁሉ ይጠ​ብ​ቃል፥ ከእ​ነ​ር​ሱም አንድ አይ​ሰ​በ​ርም።

21 የኃ​ጥእ ሞቱ ክፉ ነው ጽድ​ቅ​ንም የሚ​ጠሉ ይጸ​ጸ​ታሉ።

22 የባ​ሪ​ያ​ዎ​ቹን ነፍስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይቤ​ዣል፥ በእ​ር​ሱም የሚ​ያ​ምኑ ሁሉ አይ​ጸ​ጸ​ቱም።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos