Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 149 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሃሌ ሉያ።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አዲስ ምስ​ጋ​ናን አመ​ስ​ግ​ኑት፤ ምስ​ጋ​ና​ውም በጻ​ድ​ቃኑ ጉባኤ ነው።

2 እስ​ራ​ኤል በፈ​ጣ​ሪው ደስ ይለ​ዋል፥ የጽ​ዮ​ንም ልጆች በን​ጉ​ሣ​ቸው ሐሤ​ትን ያደ​ር​ጋሉ።

3 ስሙን በደ​ስታ ያመ​ሰ​ግ​ናሉ፥ በከ​በ​ሮና በበ​ገና ይዘ​ም​ሩ​ለ​ታል።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሕ​ዝቡ ደስ ብሎ​ታ​ልና፥ የዋ​ሃ​ን​ንም በማ​ዳኑ ከፍ ከፍ ያደ​ር​ጋ​ልና።

5 ጻድ​ቃን በክ​ብሩ ይመ​ካሉ፤ በመ​ኝ​ታ​ቸ​ውም ላይ ሐሤ​ትን ያደ​ር​ጋሉ።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በጕ​ሮ​ሮ​አ​ቸው ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ታል፤ ሁለት አፍ ያለ​ውም ሰይፍ በእጁ ነው፥

7 በአ​ሕ​ዛብ ላይ በቀ​ልን ያደ​ርግ ዘንድ፥ ሕዝ​ቡ​ንም ይዘ​ል​ፋ​ቸው ዘንድ፤

8 ንጉ​ሦ​ቻ​ቸ​ው​ንም በእ​ግር ብረት፥ አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ው​ንም በሰ​ን​ሰ​ለት ያስ​ራ​ቸው ዘንድ፤

9 የተ​ጻ​ፈ​ውን ፍርድ በእ​ነ​ርሱ ላይ ያደ​ርግ ዘንድ። ይህች ክብር ለጻ​ድ​ቃኑ ሁሉ ናት።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos