Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 142 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ልጁ ባሳ​ደ​ደው ጊዜ የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 አቤቱ፥ ጸሎ​ቴን ስማ፥ በእ​ው​ነ​ትህ ልመ​ና​ዬን አድ​ምጥ፥ በጽ​ድ​ቅ​ህም መል​ስ​ልኝ።

2 ሕያው ሁሉ በፊ​ትህ አይ​ጸ​ድ​ቅ​ምና ከባ​ሪ​ያህ ጋር ወደ ክር​ክር አት​ግባ።

3 ጠላት ነፍ​ሴን ከብ​ቦ​አ​ታ​ልና ሕይ​ወ​ቴ​ንም በም​ድር ውስጥ አዋ​ር​ዶ​አ​ታል፥ ቀድሞ እንደ ሞተ ሰው በጨ​ለማ አኖ​ሩኝ።

4 ሰው​ነቴ በላዬ አለ​ቀ​ች​ብኝ፥ ልቤም በው​ስጤ ደነ​ገ​ጠ​ብኝ።

5 የቀ​ድ​ሞ​ውን ዘመን ዐሰ​ብሁ፥ ሥራ​ህ​ንም ሁሉ አነ​በ​ብሁ፤ የእ​ጅ​ህ​ንም ሥራ አነ​ብ​ባ​ለሁ።

6 እጆ​ቼን ወደ አንተ ዘረ​ጋሁ፤ ነፍ​ሴም እንደ ምድረ በዳ አን​ተን ተጠ​ማች።

7 አቤቱ፥ ፈጥ​ነህ ስማኝ፥ ሰው​ነቴ አል​ቃ​ለች፤ ፊት​ህ​ንም ከእኔ አት​መ​ልስ፥ ወደ ጕድ​ጓ​ድም እን​ደ​ሚ​ወ​ርዱ አል​ሁን።

8 አቤቱ፥ አን​ተን ታም​ኛ​ለ​ሁና፥ በማ​ለዳ ምሕ​ረ​ት​ህን አሰ​ማኝ፤ አቤቱ፥ ነፍ​ሴን ወደ አንተ አን​ሥ​ቻ​ለ​ሁና የም​ሄ​ድ​ባ​ትን መን​ገድ ምራኝ።

9 አቤቱ፥ ወደ አንተ ተማ​ጽ​ኛ​ለ​ሁና ከጠ​ላ​ቶቼ አድ​ነኝ።

10 አቤቱ፥ አንተ አም​ላኬ ነህና ፈቃ​ድ​ህን ለማ​ድ​ረግ አስ​ተ​ም​ረኝ፤ ቅዱስ መን​ፈ​ስ​ህም በጽ​ድቅ ምድር ይም​ራኝ።

11 አቤቱ፥ ስለ ስምህ ሕያው አድ​ር​ገኝ፤ ስለ ጽድ​ቅ​ህም ነፍ​ሴን ከመ​ከ​ራዋ አው​ጣት።

12 በፈ​ቃ​ድህ ጠላ​ቶቼን አጥ​ፋ​ቸው፥ እኔ ባሪ​ያህ ነኝና ነፍ​ሴን የሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቁ​አ​ትን ሁሉ አጥ​ፋ​ቸው።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos