Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 134 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሃሌ ሉያ።

1 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስም አመ​ስ​ግኑ፤ እና​ንተ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪ​ያ​ዎች ሆይ፥ አመ​ስ​ግ​ኑት።

2 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ውስጥ፥ በአ​ም​ላ​ካ​ችን ቤት አደ​ባ​ባይ የም​ት​ቆሙ።

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቸር ነውና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ፤ ለስሙ ዘምሩ፥ መል​ካም ነውና፤

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያዕ​ቆ​ብን ለራሱ፥ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ርስቱ እን​ዲ​ሆን መር​ጦ​ታ​ልና፤

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታላቅ እንደ ሆነ፥ አም​ላ​ካ​ች​ንም ከአ​ማ​ል​ክት ሁሉ እን​ዲ​በ​ልጥ አው​ቃ​ለ​ሁና።

6 በሰ​ማ​ይና በም​ድር፥ በባ​ሕ​ርና በጥ​ል​ቆ​ችም ሁሉ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የወ​ደ​ደ​ውን ሁሉ አደ​ረገ።

7 ከም​ድር ዳር ደመ​ና​ትን ያወ​ጣል፤ ለዝ​ናም ጊዜም መብ​ረ​ቅን አደ​ረገ፤ ነፋ​ሳ​ት​ንም ከመ​ዛ​ግ​ብቱ ያወ​ጣል።

8 የግ​ብ​ፅን በኵር ልጆች ሁሉ ከሰው ጀምሮ እስከ እን​ስሳ ድረስ ገደለ።

9 ግብፅ ሆይ፥ በመ​ካ​ከ​ልሽ በፈ​ር​ዖ​ንና በባ​ሪ​ያ​ዎቹ ሁሉ ላይ ተአ​ም​ራ​ት​ንና ድን​ቅን ሰደደ።

10 ብዙ አሕ​ዛ​ብን መታ፥ ብር​ቱ​ዎ​ች​ንም ነገ​ሥ​ታት ገደለ።

11 የአ​ሞ​ራ​ው​ያ​ንን ንጉሥ ሴዎ​ንን፥ የባ​ሳ​ን​ንም ንጉሥ ዐግን፥ የከ​ነ​ዓ​ንን ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ገደለ፤

12 ርስት ምድ​ራ​ቸ​ው​ንም ለሕ​ዝቡ ለእ​ስ​ራ​ኤል ርስት አድ​ርጎ ሰጠ።

13 አቤቱ፥ ስምህ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነው፥ መታ​ሰ​ቢ​ያ​ህም ለልጅ ልጅ ነው፤

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሕ​ዝቡ ይፈ​ር​ዳ​ልና፥ ባሪ​ያ​ዎ​ቹ​ንም ያጽ​ና​ና​ልና።

15 የአ​ሕ​ዛብ ጣዖ​ታት የብ​ርና የወ​ርቅ፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው።

16 አፍ አላ​ቸው፥ ግን አይ​ና​ገ​ሩም፤ ዐይን አላ​ቸው፥ ግን አያ​ዩም፤

17 ጆሮ አላ​ቸው፥ ግን አይ​ሰ​ሙም፤ አፍ​ንጫ አላ​ቸው፥ ግን አያ​ሸ​ቱም፤ እጅ አላ​ቸው፥ ግን አይ​ዳ​ስ​ሱም፤ እግር አላ​ቸው፥ ግን አይ​ሄ​ዱም፤ በጕ​ሮ​ሮ​አ​ቸው አይ​ና​ገ​ሩም፥ እስ​ት​ን​ፋ​ስም በአ​ፋ​ቸው የለም።

18 የሚ​ሠ​ሩ​አ​ቸው ሁሉ፥ የሚ​ታ​መ​ኑ​ባ​ቸ​ውም ሁሉ እንደ እነ​ርሱ ይሁኑ።

19 የእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖች ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፤ የአ​ሮን ወገ​ኖች ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፤

20 የሌዊ ወገ​ኖች ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈ​ሩት ሆይ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት።

21 በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ያ​ድር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጽ​ዮን የተ​መ​ሰ​ገነ ነው።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos